Get Mystery Box with random crypto!

"ልጆቼ የቤተክርስቲያንን ነገር አደራ"

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetgen — "ልጆቼ የቤተክርስቲያንን ነገር አደራ"
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewnetgen — "ልጆቼ የቤተክርስቲያንን ነገር አደራ"
የሰርጥ አድራሻ: @ewnetgen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.42K
የሰርጥ መግለጫ

@Dan12bot
ለአስተያየትዎ ይህን ይጠቀሙ እናመሠግናለን

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-13 15:13:52 /ከሰማሁት/
ፍቅር ከሌለ ቀፎ ነው፡-
ሰላም ሰላም የሚባለው በአፍ አይደለም
ሰላማዊ ሰልፍ እያሉ አስፓልት ሲጠርጉ ከመዋል
በቤተ ክርስቲያን ተሰብስቦ እግዚኦ ማለት ይበልጣል
ግን መጀመሪያ እርስ በርሱ ይታረቅ
እርስ በርሱ ሰላም ከሆነ ሰላም መሪ ይሰጣል ጌታ
ህዝቡ ጠማማ ከሆነ የባሰ ያመጣል፡፡
እግዚአብሔር ስላምና ፍቅርን አንድነትን ይስጠን
@Ewnetgen
341 views12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 23:05:05 "ገንዘብን የሚቀሙ በተወገዙባት ምድር ሕይወትን የሚቀሙ ፣ የሰው ዘር ቅነሳ የሚያደርጉ ግፈኞች ሲንጎማለሉ ማየት ያሳዝናል" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

ሰኔ 16 ቀን 2014 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)


++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

የኢትዮጵያው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ በዛሬው ዕለት በልዩ ጽ/ቤታቸው አማካይነት ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ገንዘብን የሚቀሙ በተወገዙባት ምድር ሕይወትን የሚቀሙ ፣ የሰው ዘር ቅነሳ የሚያደርጉ ግፈኞች ሲንጎማለሉ ማየት ያሳዝናል ሲሉ ገልፀዋል።


ቅዱስነታቸው ስሜትን በሚወርር ልብን በሚያሳዝን፣ ጉልበትን በሚሰብር ኀዘን ውስጥ ላሉት ወገኖቻችን ፤ ትናንት ባለ ብዙ ቤተሰብ ዛሬ ሌጣ ለሆኑት ፣ የክብር ሞትና መቃብር ለተነፈጉት ሰው ሆነው በሰው ለተገፉት ፣ ኢትዮጵያዊ ሁነው በኢትዮጵያውያን ለተሠዉት ፣ አገር ሳላቸው እንደ ባዕድ ለተቆጠሩት ፣ ለደከሙበት ምድር በወርቅ ፈንታ ሰይፍ ለተከፈሉት ልጆቻችን እግዚአብሔር ያጽናችሁ በማለት ፣ የሞቱትንም ደመ አቤልን ያከበረ አምላክ ደማቸውን እንዲመራመር እንለምናለን ብለዋል።

ብዙ መልካም ቃላት በሚነገሩበት፣ የጥበብ ድምፆች በሚያስተጋቡበት ፣ መሠረት ፈርሶ ለጉልላት ጌጥ በምንጨነቅበት በዚህ ዘመን ፣ እንዴት ካለው ጊዜ ደረስን?" ማለት መመጻደቅ ባይሆን ኖሮ የሚባልበት ወቅት ሁኖ አግኝተነዋል። ትናንት ገንዘብን የሚቀሙ “እንዴት የሰውን ልፋት ይወስዳሉ? ተብለው በተወገዙበት ምድር ሕይወትን የሚቀሙ፤ የሰው ዘር ቅነሳ የሚያደርጉ ግፈኞች ሲንጎማለሉ ማየት ያሳዝናል። ንጹሐን ወገኖቻችን እግዚአብሔር በሰጣቸው ማንነት ብቻ ሲሞቱ ስናይ የዝቅታችንና የመውደቃችን ልክ ማጣት ጎልቶ ይታያል። በርግጥ የሞቱት ወገኖቻችን ሰማዕታት ናቸውና ቤተ ክርስቲያን ትዘክራቸዋለች። ሰማዕት ስለ እግዚአብሔር ብሎ የሚሞት ነው። እነዚህም ወገኖቻችን እግዚአብሔር በሰጣቸው ማንነት ፣ ለምን እንዲህ ተፈጠራችሁ ተብለው የሞቱ ናቸውና ሰማዕታት እንላቸዋለን። ገዳዮችም ቀጥተኛ የእግዚአብሔር ተቃዋሚዎች ናቸው ነው ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ

በወለጋና በጋምቤላ የአገራችን ክፍል የደረሰውን አሰቃቂ የወገኖቻችን ግድያ ስሰማ እንደ ወትሮው ልቤ በታላቅ ኀዘን ተመትቷል። በመላው የሀገራችን ክፍልም ክረምቱ ዓመት ከዓመት ጠሉም የንጹሐን እንባ ሁኖ፣ “ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ" ያለው የጌታችን ቃል ደርሶ እያየን ነው። ጆሮ ከአቅሙ በላይ በሚሰማበት በዚህ ዘመን ያላችሁ ልጆቻችን አሁንም ልባችሁን እንደ ነቢዩ ዳዊት በእግዚአብሔር አበርቱ። ጠብና ክርክሩ እግዚአብሔር ከፈጠረው ሰውነት ጋር ነውና እግዚአብሔር ፍርድ እንደሚሰጥ እናምናለን። የሃይማኖት አባቶችም የምናስተምረው ሕዝብ አልቆ ማንን ልናስተምር መሆኑን ደግመን ማሰብ ያስፈልገናል። አገራችን ኢትዮጵያ የሚያስከብሯትን መሪዎች አሁንም እየተጣራች ነውና መንግሥትና ሕዝብ ግፍን በተግባር ማውገዝ ያስፈልጋቸዋል። ነቢዩ ኤርምያስ በኀዘን ልቅሶው:- የመቅደሱ ድንጋዮች በጐዳና ሁሉ ራስ ተበተኑ ብሏል ሰቆቃ ኤር 4፡1/ የሰው ልጅ ሕያው የእግዚአብሔር መቅደስ ነውና በየስፍራው ሲገደልና ቀባሪ ሲያጣ ስናይ ከነቢዩ ጋር ለማልቀስ እንገደዳለን።

ጊዜው እየረፈደ፣ ሞትም ዜና እየሆነ፣ ዜጋም ክብሩን እያጣ፣ ሥጋትም ገዥ እየሆነ የምንቀጥልበት ጊዜ እንዲያበቃም ታላቅ ጥሪያችንን በሕያው እግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን ሲሉም ቅዱስነታቸውን አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

#Ethiopia 
#Tewahedo_Media_Center
#TMC
669 viewsedited  20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 23:16:02
ያለውና የነበረው የሚመጣው

አንዲት በአረብ ሀገር የእስልምና እምነት ተከታይ የነበረች ሴት ወደ አንድ የግብፅ ካህን ጋር በመሄድ አባቴ አጥምቁኝ አለቻቸው።

ካህኑም አንቺ የእስልምና እምነት ተከታይ ነሽ
እናም አስቀድመሽ ልትማሪ ልታምኚ ይገባል አሏት
እርሷም እኔ ክርስቲያን ነኝ ሁሉን ነገር ራሱ ክርስቶስ አስተምሮኛል አንድታጠምቁኝ እፈልጋለሁ አለቻቸው።

ካህኑም በመገረም ለመሆኑ በማን ስም ነው የምትጠመቂው አሏት?

በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም

አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማናቸው?

አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ልዩ ሦስትነት ያላቸው አንድ አምላክ ነው።
"አብ አምላክ ነው። ወልድ አምላክ ነው። መንፈስ ቅዱስ አምላክ ነው። ግን ሦስት አምላክ አይባልም አንድ ልዩ አምላክ ነው። አለች

"ይህን እንዴት አወቅሽ?

በራዕይ ዩሐንስ ላይ፦
“ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ፦ አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል።” ራእይ 1፥8

ይህ ስለ ጊዜ የተነገረ ነው፦

ትላንትም ጊዜ ነው። ዛሬም ጊዜ ነው። ነገም ጊዜ ነው። ነገር ግን ትላንት ዛሬ አይደለም። ዛሬም ትላንት ወይንም ነገ አይደለም። ነገም ትላንት ወይንም ዛሬ አይደለም። ሦስቱም ግን ጊዜ ናቸው። ነገር ግን በአንድ ላይ የተጨፈለቁ አይደሉም። ትላንት ለብቻ ነው፣ ዛሬ ለብቻው ነው።፣ነገም ለብቻው ነው።

እንዲሁም፦

አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ናቸው።
ነገር ግን አብ፥ ወልድ አይደለም፣ መንፈስ ቅዱስም አብ አይደለም። ሦስቱም በህልውና አንድ አምላክ ሆነው ይኖራሉ እንጂ።

እንዲህ አድርጎ ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮኛል አለቻቸው።

ካህኑም እጅግ በመደነቅ ከልብ ለሚፈልጉት ለልበ ንፁሐን ምሥጢርን የሚገለጥ ክርስቶስን እያደነቁ አጠመቋት።
565 views20:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 23:27:02 #ጠቃሚ ምክር!

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ለደካሞች ትጉላቸው " ብሎ በተናገረው መሠረት ምንጊዜም የሰዎችን ሞራልና መንፈስ ለመጠበቅ እንሞክር። [1ኛ ተሰ 5*14] አንድን ሰው ሲቆጡት፤ ሲወቅሱትና ፤ትህትናን ሲነፍጉት ብትመለከቱት እርሱን ከጎናችሁ አድርጋችሁ የሚገባውን በእርሱ ስም ተናገሩለት። በእርግጥም ይህ ሰው ይህንን ታላቅ ሥራችሁን በእድሜው ዘመን ሙሉ አይረሳውም። ይህ ማለት ደግሞ በፍቅርና በቸርነት በተሞሉ ታታላላቅ ልቦናዎች መንፈሳቸው ለደከመ ሰዎች የተደረገ ታላቅ ሥራ ነው። በኃጢአት የተተበተበ አንድ ሰው ብታገኙ ከዚህ ነፃ አውጡት እንጂ አትገስጹት።
@Ewnetgen
በአንድ ወቅት አንድ ወጣት ልጅ የገባበት ውኃ ሊያሰጥመው ሲል ራሱን ለማዳን በመፍጨርጨር ላይ ሳለ በዚያ የሚያልፍ አንድ ሰው "ልጄ ሆይ ዋና ሳትችል እንዴት እዚህ ባሕር ውስጥ ልትገባ ቻልክ! ?" እያለ ሲቆጣው ልጁ "በእርግጥ ተሳስቻለሁ ወደዚህ ባሕር የገባሁበትን ምክንያት እንድነግርህ ግን በመጀመሪያ ከሞት አድነኝ " ብሎ መልሶለታል። እናንተም ልክ እንደዚህ ሰውዬ መሆን የለባችሁም። ማንንም ሰው ሲወድቅ ብትመለከቱት አትገስጹት ይልቁንም። ተስፋ ስጡት። " እኔ ብዙ ጠቃሚ ምክሮች መክሬሃለሁ አንተ ግን አልተጠቀምክባቸውም ስለዚህ ከባድ መከራ ቢደርስብህ አይቆጨኝም " ብለን አንናገር።
@Ewnetgen
የሐዋርያው ቃል በንቃት አድምጡ። "...... ለደካሞች ትጉላቸው ሰውን ሁሉ ታገሱ" [1ኛ ተሰ 5*14] ። ሥሩን የሰደደ ኃጢአትን ነቅሎ ለመጣል ጊዜና ትዕግስት ስለሚጠይቅ እግዚአብሔር እንደነዚህ ያሉትን ደካሞች በጸጋው እስኪጎበኛቸው ነጻ እስኪያወጣቸው ድረስ ትዕግስት አድርጉላቸው። አንተም ተፈጥሮህ ከእነርሱ ጋር ተመሳሳይ ስለሆነ ከዚህ የሚከተለውን የሐዋርያውን ቃል ዘወትር ከፊትህ አስቀድም። " ከእነርሱ ጋር እንደ ታሰረ ሆናችሁ እስሮችን አስቡ የተጨነቁትን ደግሞ ራሳችሁ ደግሞ በሥጋ እንዳለ ሆናችሁ አስቡ ።[ዕብ 12*3] ።
#የእግዚአብሔርን_ሕዝብ_ተስፋ_ለማስቆረጥ_የተጉትን_ሰዎች_እግዚአብሔር_ወደ_ተስፋይቱ_ምድር_እንዲገቡ_አልፈቀደላቸውም።
እግዚአብሔር ሕዝቡን ".....በኃይል ከእኛ ይበረታሉና በዚህ ሕዝብ ላይ መውጣት አንችልም...... ያየናቸው ሰዎች ሁሉ ረጃጅም ሰዎች ናቸው. .... እኛም በዓይናችን ግምት እንደ አንበጣዎች ነበርን " በማለት ሊያዳክሙት የነበሩትን ሰዎች ገድቧቸዋል ። [ዘኁ13*31-33]።
እናንተ ግን አንድ ሰው ኃጢአተኛ ወይም ደካማ ቢሆንም እንኳ በሕይወቱ ውስጥ መልካም ጎኑን በመፈለግ አውጥታችሁ እነዚያ ባሕርያቱን አሞግሱለት። ኢየሱስ ክርስቶስ ለሳምራዊቷ ሴት ያደረገው እንደዚህ ነው። " ባል የለኝም በማለትሽ መልካም ተናገርሽ. ..."በዚህ እውነት ተናገርሽ "[ዮሐ 4*17እና 18] ።ይህ ውዳሴ ሴቲቱ ኃጢአቷን እንድትናዘዝ ስላደረጋት ለንስሓ ትበቃ ዘንድ ጌታ አሸንፏታል። አንዱ ሰው ሌላው ሸክሙን በሚያቀሉለት በቅዱሳት መጻሕፍት ታሪኮች ሲበረታታ ሌላው ደግሞ ስለ እግዚአብሔር ጸጋና ሥራ ሲነገረው ይበረታታል። ከዚህ ሌላ ስህተቶቹን ሁሉ በመርሳት የሚበረታታ ሰው ይኖራል። ለተፈጸመ ስህተት ሁሉ ቁጣን ማቅረብ ግን ወደ ተስፋ መቁረጥ ያደርሳል።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ እንዳስተማሩት! !
@Ewnetgen @Danbicha @Dan12bot
529 views20:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 14:55:57 @Dan12bot

ለአስተያየትዎ ይህን ይጠቀሙ እናመሠግናለን

@Danbicha
ሀሳብ አስተያየት አሎት

415 views11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 14:44:33 ኃጢአቷን የምትጽፈዉ ሴት
አንዲት ሴት ነበረች ኃጢአቷን የምትጽፍ
ልቧ በኃጢአት የሰከረ ለኃጢአትም ተገዥ የሆነች ይች ሴት የተለያየ ኃጢያት የምትሰራ ናት ትዘሙታለች፣ ትዋሻለች፣ ታማለች፣ ተሰርቃለች፣ ትገድላለች፣ በአል ትሽራለች፣ በትእቢት የተሞላች ሴት ናት ልቧ ኃጢአት ነበር። ነገር ግን የምትሰራዉን ኃጢአቷን ሁሉ እየጻፈች ታስቀምጥ ነበር።
ከእለታት አንድ ቀን የጻፈችዉን ኃጢአቷን ብታየዉ ስንክሳር አክሎ ተመለከተችዉ ስንክሳር ማለት በ365 ቀኖች የሚለዉ የቅዱሳን ታሪክ ሰብስቦ የያዘ ትልቅ መጽሐፍ ነዉ። የዚች ሴትም ኃጢአትም ይህን አክሎ ነበር እንዳየችዉ ደነገጠችና ኃጢአቷን ተሸክማ አባት ወደ አለበት ወደ አንጾኪያ ሄደች አባ ባስልዮስን አገኘችዉ አባቴ በዚህ ያለዉ ኃጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችዉ።
አባ ባስልዮስም ይፋቅልሽ አላት ገልጣ ብታሳየዉ ሁሉ ተፍቆ አንዲት ኃጢአት ብቻ ቀርታ አየቻት። በጣም ከባድ ኃጢአት ነበረች ሊፈሩዋት የምትከብድ ሊነግሯት የምታሳፍር ነበረች አባቴ ይችሳ አለችዉ አባ ባስልዮስም ይችን ኃጢአትሽንስ ማስተሰረይ የሚችል ልጄ ቅዱስ ኤፍሬም ነዉ ሂደሽ ለእርሱ ንገሪዉ አላት።
አባ ባስልዮስ ይሄን ያላት ኃጢአቷን መፋቅ አቅቶት አይደለም የራሱ ክብር ከሚገልጥ የቅዱስ ኤፍሬም ክብር እንዲገለጥ ፈልጎ ነዉ። ደግሞም ስትመላለስ ንስሐ እንዲሆናት ጭምር ነዉ።
እሷም አባ ባሰስልዮስ እንዳላት ቅዱስ ኤፍሬም ወዳለበት ወደ ሶሪያ ሄደች በባዶ እግሯ እንቅፋቱ እየመታት እሾሁ እየወጋት እግሯ ሲደማ ልብሷን ቀዳ እየጠመጠመች ተጉዛ ከቅዱስ ኤፍርም ደረሰች።
አባቴ በዚህ ያለዉ ኃጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችዉ ቅዱስ ኤፍሬም ግን ይሄ ለኔ አይቻለኝም ለአባቴ ለአባ ባስለዮስ እንጂ አላት ቅዱስ ኤፍሬም ግን ኃጢአቷን መደምሰስ አቅቶት አይደለም በፈሊጥ ቀኖና ሲሰጣት እንጂ ስትመላለስ ኃጢአቷ እንዲቀልላትም ነዉ። ሂደሽ ለአባ ባስለዮስ ንገሪዉ ይደመስስልሻል አላት እሷም አግኝቸዉ እኮ አይሆንልኝም ብሎ ወደ አንተ ልኮኛል ሳትል እሽ ብላ መንገድ ስትጀምር እንደ ቀድሞዉ በህይወት አታገኝዉም ሙቶ ካህናት ሊቀብሩት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይዘዉት ሲሄዱ ታገኝዋለሽ ሳትጠራሪ የተጻፈዉ ኃጢአትሽን ከአስክሬኑ ላይ ጣይዉ አላት እሷም እሽ ብላ ሄደች የቀኑ ሙቀት የሌሊቱ ብርድ እያሰቃያት ደረሰች ሙቶ ካህናት ፍትሀት እየፈቱት አየች።
የእግዚአብሔር አገልጋይ ባስልዮስ ሆይ የባሪያህን ኃጢአት ደምስስልኝ ብላ ከአስክሬኑ ላይ ጣለችዉ አስክሬኑም ድምጽ ወጥቶ ኃጢአትሽ ተደምስሶልሻል አላት ገልጣ ብታይ ተደምስሶላታል። አምላኳን አመሰገነች በደስታ ዘመረች በዚህ በኋላ ዓለምን ንቃ ገዳም ገብታ መኖር ጀመረች።
እንደዚች ሴት ኃጢአቱን የሚያስታዉስ ማነዉ?
ወደ ካህን ሂዶ ንስሐ የገባስ ስንቱ ነዉ?
ስለ ኃጢአቱ በረሃ የተከራተተ ማን ይሆን?
የዚችን ሴት መጨረሻ ያሳመረ የሁላችንም መጨረሻ ያሳምርልን ኃጢአቷን የደመሠሠ የሁላችንም ኃጢአት ይደምስስልን!
ለንስሐ የሚሆን ፍሬ አድርጉ
የዉዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ @Ewnetgen
563 views11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 14:44:13
355 viewsedited  11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 11:16:32 (ልብን የሚነካ ፀሎት፣ ሁሌ ይህንን እያልን እንለምነው) በአቡነ ሺኖዳ

ስለጸሎት ምክር

"መልካም ነገሮች ከሚባሉት መካከል ተጠቃሽ የሚሆነው አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል አጥብቆ መያዙ እና መጠበቁ ነው። እግዚአብሔር ብዙ ቃል ገብቷል እና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ግልፅና ታማኝ ነው። እናም ቃሉን አያጥፍም። የእርሱን ቃል ይዛችሁ ከእርሱ ጋር ተነጋገሩ። " ቃል የገባህልንን መች ነው የምትፈፅምልን" በሉት።
ቃልህን ይዤ እጠይቅሀለው “አዲስ ልብን እሰጣችኋለው” ብለሃል ፣ ታዲያ የታለ አዲሱ ልብ? እኔ ራሴን ስመለከተው የድሮ ልቤ እንዳለ ነው። የትናንትናው መጥፎ ጠባይ ልክ እንደ ትናንትናው ነው። የታለ ታዲያ አዲስ ልብ እሰጥሃለሁ ያልከኝ? እኔ ማወቅ እፈልጋለው፣ ከውስጥ እንድትቀይረው እንድትሰማው እፈልጋለው፣ እኔ አስቸገርኩህ አንተ አስተካክለኝ፣ ሥራብኝ፣ ደረቅ መሆኔን አስተካክልልኝ። ስህተት አለብኝና ስህተቴን አስወግደው። ድርቅና አለብኝና ድርቅናዬን አስወግደው ። ኃጢያአት አለብኝና ኃጢአቴን አስወግደው። ጌታ ሆይ እኔ ውስጥ ሥራ ። እናም ውስጤን አንጻው። መጋዙን መዶሻውን አንሳው። ሥራብኝ ይህ መጥፎ እንጨት የተባለውን ላንተ ወንበር አርገው" በሉት።
አንዳንድ ሰዎች ደካማ መሆናቸውን ሲያውቁ አለመቻላቸውን እና መውደቃቸውን ሲያረጋግጡ እግዚአብሔር ወደ ሕይወታቸው እንዲገባ ከመለመን ይልቅ እግዚአብሔርን ይቀየሙታል እና ይጮሀሉ" ለምንድን ነው እግዚአብሔር ብቻዬን የተወኝ? በቃ ከአሁን በኋላ እግዚአብሔርን አላቅም! ቤተክርስቲያን አልሄድም ! ንስሐ አልገባም ! አልቆርብም !" ይላሉ ። ይህ ምንድን ነው? ጌታን ከመለመን ይልቅ መቃወም ይሻላልን?
እስቲ አስተዋይ ሰው እንሁን!
ከእግዚአብሔር ጋር ሆነህ ተፋለም ፣ ታሸንፋለህ እና ታልፋለህም። እግዚአብሔርን እንዲህ ብለህ ጠይቀው...
"ጌታ ሆይ አጋዥ ትባላለህ ፤ አጋዥነትህ የት አለ? ና አግዘኝ። አዳኝ ትባላለህ፤ የት አለ ማዳንህ? ና አድነኝ። ምንም ነገር አይሳንህም ትባላለህ እኔን ማዳን አይሳንህም፥ ያለምክንያት ‘ምንም የማይሳነው’ አንልህምና። ጌታ ሆይ፥ እኔ አንድ ችግር ነኝ። ፊት ለፊትህ ቀርቤያለው መንፈስህን አኑርብኝ። ምንም አይሳንህም እና እኔን ሥራኝ። እምነትህ ደካማ ነው ካልከኝ ፥ ጠንካራ አድርገው። ልቤ ቆሽሿል እና አፅዳልኝ። ሙሴ ጸሊምን እና ማርያም መግደላዊትን እንዳስተካከልካቸው እኔንም አስተካክለኝ። አንተ የምትለው "ወደ እኔ የመጣውን ወደ ውጪ አላስወጣውም " ነው ... ይኸው ወደ አንተ መጥቻለው ባዶ እጄን አትላከኝ ። ጌታ ሆይ የበጎ ነገር ፈጣሪ ትባላለህ እንዲ ከሆነ በእኔ ውስጥ በጎ ነገርን ስራ ።

ከብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ስብከት የተቀነጨበ @Ewnetgen
404 views08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 11:16:32 (ልብን የሚነካ ፀሎት፣ ሁሌ ይህንን እያልን እንለምነው) በአቡነ ሺኖዳ

ስለጸሎት ምክር

"መልካም ነገሮች ከሚባሉት መካከል ተጠቃሽ የሚሆነው አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል አጥብቆ መያዙ እና መጠበቁ ነው። እግዚአብሔር ብዙ ቃል ገብቷል እና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ግልፅና ታማኝ ነው። እናም ቃሉን አያጥፍም። የእርሱን ቃል ይዛችሁ ከእርሱ ጋር ተነጋገሩ። " ቃል የገባህልንን መች ነው የምትፈፅምልን" በሉት።
ቃልህን ይዤ እጠይቅሀለው “አዲስ ልብን እሰጣችኋለው” ብለሃል ፣ ታዲያ የታለ አዲሱ ልብ? እኔ ራሴን ስመለከተው የድሮ ልቤ እንዳለ ነው። የትናንትናው መጥፎ ጠባይ ልክ እንደ ትናንትናው ነው። የታለ ታዲያ አዲስ ልብ እሰጥሃለሁ ያልከኝ? እኔ ማወቅ እፈልጋለው፣ ከውስጥ እንድትቀይረው እንድትሰማው እፈልጋለው፣ እኔ አስቸገርኩህ አንተ አስተካክለኝ፣ ሥራብኝ፣ ደረቅ መሆኔን አስተካክልልኝ። ስህተት አለብኝና ስህተቴን አስወግደው። ድርቅና አለብኝና ድርቅናዬን አስወግደው ። ኃጢያአት አለብኝና ኃጢአቴን አስወግደው። ጌታ ሆይ እኔ ውስጥ ሥራ ። እናም ውስጤን አንጻው። መጋዙን መዶሻውን አንሳው። ሥራብኝ ይህ መጥፎ እንጨት የተባለውን ላንተ ወንበር አርገው" በሉት።
አንዳንድ ሰዎች ደካማ መሆናቸውን ሲያውቁ አለመቻላቸውን እና መውደቃቸውን ሲያረጋግጡ እግዚአብሔር ወደ ሕይወታቸው እንዲገባ ከመለመን ይልቅ እግዚአብሔርን ይቀየሙታል እና ይጮሀሉ" ለምንድን ነው እግዚአብሔር ብቻዬን የተወኝ? በቃ ከአሁን በኋላ እግዚአብሔርን አላቅም! ቤተክርስቲያን አልሄድም ! ንስሐ አልገባም ! አልቆርብም !" ይላሉ ። ይህ ምንድን ነው? ጌታን ከመለመን ይልቅ መቃወም ይሻላልን?
እስቲ አስተዋይ ሰው እንሁን!
ከእግዚአብሔር ጋር ሆነህ ተፋለም ፣ ታሸንፋለህ እና ታልፋለህም። እግዚአብሔርን እንዲህ ብለህ ጠይቀው...
"ጌታ ሆይ አጋዥ ትባላለህ ፤ አጋዥነትህ የት አለ? ና አግዘኝ። አዳኝ ትባላለህ፤ የት አለ ማዳንህ? ና አድነኝ። ምንም ነገር አይሳንህም ትባላለህ እኔን ማዳን አይሳንህም፥ ያለምክንያት ‘ምንም የማይሳነው’ አንልህምና። ጌታ ሆይ፥ እኔ አንድ ችግር ነኝ። ፊት ለፊትህ ቀርቤያለው መንፈስህን አኑርብኝ። ምንም አይሳንህም እና እኔን ሥራኝ። እምነትህ ደካማ ነው ካልከኝ ፥ ጠንካራ አድርገው። ልቤ ቆሽሿል እና አፅዳልኝ። ሙሴ ጸሊምን እና ማርያም መግደላዊትን እንዳስተካከልካቸው እኔንም አስተካክለኝ። አንተ የምትለው "ወደ እኔ የመጣውን ወደ ውጪ አላስወጣውም " ነው ... ይኸው ወደ አንተ መጥቻለው ባዶ እጄን አትላከኝ ። ጌታ ሆይ የበጎ ነገር ፈጣሪ ትባላለህ እንዲ ከሆነ በእኔ ውስጥ በጎ ነገርን ስራ ።

ከብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ስብከት የተቀነጨበ
327 views08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 11:16:32 (ልብን የሚነካ ፀሎት፣ ሁሌ ይህንን እያልን እንለምነው) በአቡነ ሺኖዳ

ስለጸሎት ምክር

"መልካም ነገሮች ከሚባሉት መካከል ተጠቃሽ የሚሆነው አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል አጥብቆ መያዙ እና መጠበቁ ነው። እግዚአብሔር ብዙ ቃል ገብቷል እና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ግልፅና ታማኝ ነው። እናም ቃሉን አያጥፍም። የእርሱን ቃል ይዛችሁ ከእርሱ ጋር ተነጋገሩ። " ቃል የገባህልንን መች ነው የምትፈፅምልን" በሉት።
ቃልህን ይዤ እጠይቅሀለው “አዲስ ልብን እሰጣችኋለው” ብለሃል ፣ ታዲያ የታለ አዲሱ ልብ? እኔ ራሴን ስመለከተው የድሮ ልቤ እንዳለ ነው። የትናንትናው መጥፎ ጠባይ ልክ እንደ ትናንትናው ነው። የታለ ታዲያ አዲስ ልብ እሰጥሃለሁ ያልከኝ? እኔ ማወቅ እፈልጋለው፣ ከውስጥ እንድትቀይረው እንድትሰማው እፈልጋለው፣ እኔ አስቸገርኩህ አንተ አስተካክለኝ፣ ሥራብኝ፣ ደረቅ መሆኔን አስተካክልልኝ። ስህተት አለብኝና ስህተቴን አስወግደው። ድርቅና አለብኝና ድርቅናዬን አስወግደው ። ኃጢያአት አለብኝና ኃጢአቴን አስወግደው። ጌታ ሆይ እኔ ውስጥ ሥራ ። እናም ውስጤን አንጻው። መጋዙን መዶሻውን አንሳው። ሥራብኝ ይህ መጥፎ እንጨት የተባለውን ላንተ ወንበር አርገው" በሉት።
አንዳንድ ሰዎች ደካማ መሆናቸውን ሲያውቁ አለመቻላቸውን እና መውደቃቸውን ሲያረጋግጡ እግዚአብሔር ወደ ሕይወታቸው እንዲገባ ከመለመን ይልቅ እግዚአብሔርን ይቀየሙታል እና ይጮሀሉ" ለምንድን ነው እግዚአብሔር ብቻዬን የተወኝ? በቃ ከአሁን በኋላ እግዚአብሔርን አላቅም! ቤተክርስቲያን አልሄድም ! ንስሐ አልገባም ! አልቆርብም !" ይላሉ ። ይህ ምንድን ነው? ጌታን ከመለመን ይልቅ መቃወም ይሻላልን?
እስቲ አስተዋይ ሰው እንሁን!
ከእግዚአብሔር ጋር ሆነህ ተፋለም ፣ ታሸንፋለህ እና ታልፋለህም። እግዚአብሔርን እንዲህ ብለህ ጠይቀው...
"ጌታ ሆይ አጋዥ ትባላለህ ፤ አጋዥነትህ የት አለ? ና አግዘኝ። አዳኝ ትባላለህ፤ የት አለ ማዳንህ? ና አድነኝ። ምንም ነገር አይሳንህም ትባላለህ እኔን ማዳን አይሳንህም፥ ያለምክንያት ‘ምንም የማይሳነው’ አንልህምና። ጌታ ሆይ፥ እኔ አንድ ችግር ነኝ። ፊት ለፊትህ ቀርቤያለው መንፈስህን አኑርብኝ። ምንም አይሳንህም እና እኔን ሥራኝ። እምነትህ ደካማ ነው ካልከኝ ፥ ጠንካራ አድርገው። ልቤ ቆሽሿል እና አፅዳልኝ። ሙሴ ጸሊምን እና ማርያም መግደላዊትን እንዳስተካከልካቸው እኔንም አስተካክለኝ። አንተ የምትለው "ወደ እኔ የመጣውን ወደ ውጪ አላስወጣውም " ነው ... ይኸው ወደ አንተ መጥቻለው ባዶ እጄን አትላከኝ ። ጌታ ሆይ የበጎ ነገር ፈጣሪ ትባላለህ እንዲ ከሆነ በእኔ ውስጥ በጎ ነገርን ስራ ።

ከብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ስብከት የተቀነጨበ
321 views08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ