Get Mystery Box with random crypto!

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በተሳካ ሁኔታ ለመስጠት ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ የ | Ethio University

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በተሳካ ሁኔታ ለመስጠት ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ

የትምህርት ሚኒስቴር የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ፈተናውን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫውም ፈተናው በዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ የሚሰጠው፥ ባለፉት አመታት የፈተና አሰጣጡን ሲያውክ የነበረውን የፈተና ስርቆትና የሃሰተኛ መልስ ስርጭትን ለመከላከል በማሰብ መሆኑን አስታውቋል።

ለዚህም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሙሉ ዝግጅት ማድረጉን ነው የገለጸው።

ተፈታኞች በአካባቢያቸው በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናውን የሚወስዱ ሲሆን በተቀመጡ መመሪያዎች መሰረት የፈተናውን ደህንነት ለማስጠበቅ የተወሰነውን ውሳኔ አክብረው እንዲፈተኑ፤ ወላጆችም ለዚህ አላማ መሳካት አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ተጠይቋል።

(ኤፍ ቢ ሲ)