Get Mystery Box with random crypto!

ሁለት ቤተሰቦችን ያጨቃጨቀዉ ከሞት ተነሳ የተባለዉ ታዳጊ ጉዳይ እልባት ማግኘቱ ፖሊስ አስታወቀ | 🇪🇹 ኢትዮ Students

ሁለት ቤተሰቦችን ያጨቃጨቀዉ ከሞት ተነሳ የተባለዉ ታዳጊ ጉዳይ እልባት ማግኘቱ ፖሊስ አስታወቀ

በስልጤ ሁልባራግ ወረዳ ቢለዋንጃ ቀበሌ  ከአራት አመት በፊት ሞቶ ተቀብሯል የተባለዉ ታዳጊ ባቂ ሲከማ መሀመድን  ከመንገድ ላይ ያገኙት የአካባቢዉ ነዋሪዎች ነሐሴ 28 ቀን 2015 ዓ.ም  ለቤተሰቡ አስረክበዋል።

የታዳጊዉ ቤተሰቦችም  ሟች ልጃቸዉ ባቂ ስለመሆኑ አንዳችም የሚያጠራጥር ነገር እንደሌለዉ አረጋግጠዉ ተደስተው ፈጣሪ ከሞተ በኋላ አስነስቶ ህያዉ አድርጎታል ሲሉ ታዳጊዉን ተቀብለዉ እንደወትሮዉ መንከባከብ መጀመራቸዉ ተነግሮ ነበር።

በሌላ በኩል ደግሞ ከዚህ ታዳጊ ጋር ሁለንተናዊ መመሳሰል ያለዉ  አብዲ ሄራቶ አቦዬ የሚባል ልጅ ጠፍቶብናል የሚሉ  ቤተሰቦች ከሁልባራግ ወረዳ ወራበት ሻማ አከባቢ ልጃችን ነው ይሰጠን ሲሉ የመጡ ሲሆን በሁለቱ ቤተሰቦች መሀከል የይገባኛል ጥያቄ  መነሳቱም ቀደም ሲል ተገልጿል።

አሁን የሁለቱ ቤተሰቦች የይገባኛል ክርክር መቋጫ ማግኘቱ የሁልባረግ ወረዳ ፖሊስ ገልጿል።ፖሊስ ፣ዐቃቤህግና የሀገር ሽማግሌዎች ጋር በመሆን ባደረጉት ማጣራት አብዲ ሄራቶ የሚባል ልጅ ጠፍቶብናል የሚሉ ቤተሰቦች መሆኑ የሚያሳይ በእጅና በእግሩ የተነገሩ  ልዩ ምልክቶችን መኖራቸዉ በማረጋገጥ ታዳጊዉ ጠፍቶብናል ለሚሉ ቤተሰቦች ተላልፎ መሰጠቱ የሁልባረግ ወረዳ ፖሊስ ገልጿል።

ስለዚህ ከአራት አመት በፊት ሞቶ የተቀበረዉ ታዳጊ ከሞት አለመነሳቱ ህብረተሰቡ እንዲያዉቀዉ ሲል ፖሊስ አሳስቧል።

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS