Get Mystery Box with random crypto!

ግጥም እና ወግ መድብል (poem)📜📜🔈

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopianpoem1 — ግጥም እና ወግ መድብል (poem)📜📜🔈
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopianpoem1 — ግጥም እና ወግ መድብል (poem)📜📜🔈
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopianpoem1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.20K
የሰርጥ መግለጫ

የተለያዩ በመድብል ደረጃ ለንባብ የበቁ እና ያልበቁ የፍቅር ፣ የሀገር ፣የትዝታ ፣ እና ሌሎች ሀገርኛ ጣዕመ ዜማ ያላቸውን ግጥሞች ያልተሠሙ ወጎች እንዲሁም የገጣሚያንና የታዋቂ ሰዎች ታሪኮችን ያገኛሉ።ግጥም ከቃላት ስደራ በላይ የእውነትና የእምነት ውጤት ፤ የምስጢር ዋሻ ነው፡፡አባላችን ይሁኑ
@ethiopianpoem1
አሰተያየት እና ግጥሞች ካሏችሁ
👉👉 @Yoyo556

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-02-26 21:34:38 ለማለት ብቻ ነው


በፎከረው አፌ በተነሳው ልቤ
ከግንባሬ ወለል በሚታየው ላቤ
በድፍረት ታጅቦ ተንቀልቃይ ሀሳቤ
ደግሜ ሰልሼ ማልኩኝ በማተቤ
ድጋሚ ላልደግመው ላልጠራው በስሙ
በእንቅልፍ በህልም አለም ህልምን ላያልሙ
የተቸሩኝ ጆሮች ስለሱ ላይሰሙ
ማልኩኝ በአምላክ ስም
ካጠገቡ ላልደርስ በከናፍሮቼ ዳግም ጉንጩን ላልስም
ዛትኩኝ በንግግር በልሳኔ አለም
ቃላትን ጨረስኩኝ እንዳልነበር ሁሉም
ከተቀመጥኩበት ይህንን በሙሉ ዝቼ ካለሁበት
ከዛ ሳልነሳ ቦታ ባለሁበት
ይናፍቀኝ ጀመር ስለሱ ማሰቤን አልኩኝ የሙጥኝት
የዛተው አንደበት ፉከራው በሞላ ተረሳ በድንገት
ልቤ ምትት አለች በናፍቆት አጀባ በመናፈቅ ጥማት
ዛቻው መች ወረደ ከጉሮሮ መሬት
መች ደረሰ ከዛ ልቤ ካለችበት
አጥራ በፍቅሩ የራሷኑ ድንበር
አልነካ ብላ ተከልላ ነበር
ምንም ላይበግራት ዛቻ ና ፉከራ
አሁን ግን እጅ ሰታለች መውጣት አቅቷት ይሄንን ተራራ

By ሩት አምሳሉ

@ethiopianpoem1
@yoyo556
2.9K viewsYoni Mak, 18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-25 14:21:49 አልገጥምም!
ግጠሚልኝ አለኝ ግጥምን እንደቀላል፣
እንዳፋቅርለት እንዳጣላው በቃል፣
ኮከብን አርግፊ ሸምጥጠሽ ከሰማይ፣
ጨረቃ ብቻዋን ስትጨነቅ እንዳይ፣
መሬት ሆይ ትረግድ ወገቧን አስይዛ፣
ንፋስም ትውረግረግ ዛፎችን ጠምዝዛ፣
አለኝ እንደ ዘበት አለኝ እንደ ቀላል፣
መች ቢችል ኖሮ ግጠሚ ይለኛል፣
ህዋ ላይ ቀዝፌ ጠፈር ልዳስስ፣
ለጥቄም መጥቄ ሰማይ ቤት እንድደርስ፣
ከጥልቁ ውቅያኖስ ልስመጥ ከባህሩ፣
በበረህ አሸዋ ልንደድ በሀሩሩ
ብዕሬን ልሳለው ልያዘው ቀስሬ፣
ያበጠ አፈንድቼ የዛለ ወጥሬ፣
በቀለሜ ንጣብ በቃሎቼ ድርድር፣
ስሜቴ ነው ነፃ ስሜቴ ነው ድንበር፣
ጥልን የሚጠላ ፍቅርን የሚያፈቅር፣
ግጠሚ ገጠሚ አትበለኝ አልወድም፣
ግጠሚ ሲሉኝ እንደውም አልገጥምም።

sifen

@ethiopianpoem1
@yoyo556
2.7K viewsYoni Mak, 11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 21:14:20 አደይ አበባ ነው፣
በአለንጋ ጣቶችህ መሀከል ላይ ያለው፣
ሽቶ ነው መአዛህ ናርድስ የታጠነ፣
በፌትህ መልክ ላይ መናኝ ያስመነነ፣
አለም ነው ፈገግታህ በጥርሶችህ ላይ ብርሀን የተመላው፣
ስስ ከናፍርህ ዙሪያ የከበበው።

ብዬ አልሸወድኩት ራሴን በድለላ፣
ከንፈርህ ጥቁረቱ መስሏል እንደጥላ፣
በልዟል ጥርሶችህ ከሰል እንደፋቁ፣
ተፈጥሮ መልኩ አንተን እንደራቁ፣
የለም ፅጌሬዳው በጣቶችህ መሀል፣
ፍቅርን ለመግለጫ ሲጋራይዘዋል፣
እኔን እንደሳሙ እርሱንም ስመዋል...

ግና ከናፍርህ ከንፈሬን ሲስሙ፣
እንደ ንብ ናቸው ማር እንደቀሰሙ፣
ግና በተራዬ ብድራት ልመልስ ከንፈርህ ላይ ብገኝ፣
የሳምባህ ውስጥ ጭስ ጎም ሆኖ ወረረኝ፣
ጥርስህ ላይ የቀረው ቅጠል ምርቃና ከተተኝ፣
እንደዚህም ሆኖ ሳልጠጣ ብሰክር፣
ባጎበር አናቴ ለጉድ ቢወጣጠር,..

አውቃለው ሁሉንም አቅሌን አልሳትኩኝም፣
ተውልኝ ብዬ አማላድ ወዳንተ ፍፁም አላኩኝም፣
ምክንያቱም አለሜ በዚህ ሁሉ መሀል፣
ደረትህ ተከፍቶ ልብህ ሲመታ ጠልቆ ይሰማኛል፣
ስለዚህ
አትቃም!
አታጭስ!
አጠጣ! አልልም፣
ሱሴ ለሱሰኛ ሱሱንማ አይተውም።

sifen

@ethiopianpoem1
@yoyo556
2.5K viewsYoni Mak, 18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 20:52:44 ተዉ አትነካኩኝ


ተዉ አትነካኩኝ ሰውነቴ ሳስቷል :
እኔጃ ሰሞኑን ብርድ ብርድ ይለኛል :
ይሰማኛል ጬኸት በጓሮየ ዘልቆ :
በዋይታ ታጅቦ በእንባ ታጭቆ :

ተው አትነካኩኝ

ግራ እጄ ከቀኜ በድንገት ቢጣሉ :
በገዛ ምላሴ ባንደበቴ ዋሉ :
ጣት ገማ ተብሎ ለማይጣል ነገር :
ትዝብት ነው ትርፉ ተዉ እንከባበር :

ተዉ አትነካኩኝ

የማናውቀው ነገር ዓይን አውጥቶ መጣ
ያልሰማነውን ችግር አስከትሎ ጣጣ :
በግ እና ተኩላ የማይዛመዱትን ፡
ተወው ተወው አሉኝ የፈለጉት ይሁን :


ተዉ አትነካኩኝ

በረዶው እያለ ድንጋዩ ቀለጠ :
እርጉዟ ቁጭ ብላ ወንድ ልጅ አማጠ :
ችግሩ ደምኖ ስቃዩ ሲያካፋ :
ለሚያበቅለው ችግር ለማይሰጠው ተስፋ :
የዘንድሮስ ነገር አይመስልም የጤና :
አምላክ ሆይ በቶሎ ድረስልን ናና :


ግጥም


ከዮሴፍ

@ethiopianpoem1
@yoyo556
2.7K viewsYoni Mak, 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 20:46:25 (ብንያም ወጋየሁ)
...ንድፍ ወጉድፍ..
.
.
የነገዬን ንድፍ ሰራሁት : ቃሉን: ቅሉን ሰማሁት
ላይ ዛሬ:መንዝሬ : ቃኘሁት አየሁት
አሁኔ ሰጠገን ሲደገን በትላንቱ ውልቃት
ጉብታ አስለቅቆ ተባጥቆ ያገባኝ ንቃቃት
ለተስፋ አለም ነበረ ህልም ጥቃት ንቃት
ለነቂስ ቄስ ቢታወጅም
ሰው ነው እንጂ እድሜ አይጃጅም
ምን ቢጃጅም ቢደረጅም
እድሜ ሊያድም ቢዶለዱም አያረጅም
ትላንት ያልከው የከተብከው : በይበቃል ቃል የፃፍከው
ይፈርሳል
ይደርሳል ሁሉም ያልከው የካብከው
በዛሬ አምሮ ተሞሽሮ ሲደገስ ሲለገስ በቀን
እንጂ:
አይሞላም የሞላ እንጀራም : ነጥቀን ልቀን ሰቀቀን
እናም ወዳጄ የአምላክ ስጦታ ግደጄ
እንዲህ የሚል ቃል ልቀልም : ከተራመድከው ደጄ
"የነገዬን ንድፍ ሰራሁት : ቃሉን ቅሉን ሰማሁት
ላይ ዛሬ መንዝሬ : ቃኘሁት አየሁት"
የእምነት ድህነት ቃል ነው እውነት : የመታያህ ፅንፍ ገነት
ተራመድ ተላመድ ወደ እኔነት ከፍታው ላይ ከሰገነት
በትላንትህ ልድፍ ጉድፍ : ዛሬን ማሬን አታሳድፍ
አውጣ ውጣ ወደ ተስፋ ስፋ ተስፋ የነገ ንድፍ
አላለፈም ብለክ ያልከው በተራ እንደ ጎተራ ንቃቃት
ተሰንጥቆ ተወጥቆ ስስ ነፍስህን ሲያስጨንቃት
ጋሻ ባሻ ልመድ ግመድ ለከፈትከው ላልከው ጥቃት
ሩህን አታስጨንቃት ከአምላኳ አታራርቃት
ከአጥቢያ ኮከብ አታጣልቃት
ከጥጋጥግ ከልግ ከፍግ አታጣብቃት
ፍላፃ ነፃ ምርጫ ሆና ትቅና ትቃና አትጭመቃት
ል-ቀ-ቃ-ት
የሚሹት የሚያበላሹት ዘመንን የሚያመንን ትላንት ላንት
ይክሰል አመድ ስሩ ይጠመድ ዛሬን ማሬን ከሚያመክናት
ሁሉ:
በልቡ ሰሌዳ በህሊናው ጓዳ በሜዳ ሰርጓዳ ቃሌን ያቅናት
እንደኔ ትላንቴን ቅናቴን ፍቄው ንቄው ነገን ላፅናት
ተስፋ በሌለው ባለው ሙታን ሲያዝ የማዘዝ ስልጣን
ስም ልንሰይም ለእኩይ ሰብእ መስለን መጣን ያጣን ሰይጣን
በተስፋ ስፋ ነገን ቋጥር በአሉ አሉ አትጠርጥር
ዛሬህን ከትላንትህ አዛምደህ ንደህ ነገህን አታሳጥር
አታብጠርጥር
አታበጥር
ከፍጥረት ጥረት ንጠር ፍጠር አትታጠር
አ-ት-ጠ-ር-ጠ-ር
አምላክ መላክ እርከን ያልከን
ገደብ አደብ እንኩ ብለክ
አይደል ክፋት መስሎን እንጂ ይሻል"መ'ሻል"ከማለክለክ
አንዱን ማምለክ
እናም ወዳጄ የአምላክ ውላጅ ግዳጄ
እንዲህ የሚያልም ቃል ልቀልም ከተራመድከው ደጄ
"የነገዬን ንድፍ ሰራሁት ቃሉን ቅሉን ሰማሁት
ተስፋ ሁሉን ይሰፋ ዘንድ ተሰጥቷልና ለየሁት።"
(ሩህ ብሩህ)
''''''''''''''''';;;;;;;;;;;;;;;;;''''''''''''''''''';;;;;;;;;;;;;;;

@ethiopianpoem1
@yoyo556
2.6K viewsYoni Mak, 17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 06:50:07 :የቀድሞ ትዝታዬ ፤ የወደፊት ሕልሜ!!

ያኔ ጠዋት
ያኔ ጥንት
ገና ስንተያይ አይኖቻችን ፈዘው
ልብሽ ከልቤ ጋር አፍ ለአፍ ገጥመው
አወጋን እጅጉን እሸት የሆነውን
ለጊዜያዊ ሳይሆን አይተን የቀጣዩን
...
በብሩዕ ቀን ብሩዕ ሳቅሽን ይዤ
ተስፋ ሚባለውን ፍፁም ተመርኩዤ
ብሄድ ብትሄጂ ብለይሽ ብትለይኝ
አልጠፋም ከልቤ ይዘሽው ቦታሽን
...
ሳንገናኝ ቢያልፉ ቀናቶች አመታት
"ሀ"ብለን እንደገና ባንበላው "ያን" እሸት
አሁንም ነገም ከነገ ወዲያም
ከቶ ባንገናኝ በአንድም በሌላም
ሁነሽ ትኖሪያለሽ የወደፊት ሕልሜ
ያ'ሳቤ አንድ አካል የልብ መልሕቄ!
ሁነሽ ትቆያለሽ የሕልሜ ዳርቻ
ሰርክ እንዳስብሽ አንቺን አንቺን ብቻ!!!

ፃፍኩት 28/05/2013 ቅዳሜ ከሰዓት!
"ሁለ-ገብ" የተሰኘው ግጥሜ

@ethiopianpoem1
@yoyo556
2.1K viewsYoni Mak, 03:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 06:47:50 የጽድቅ ገበያ
========

እህል ተሸመተ...ጎታ ተከተተ
ልብስም ተሸመተ...ሳጥን ተከተተ
ቤትም ተገነባ... በንፁሀን እንባ
ድግሱም ደመቀ...
ቢሸሹት የማይሸሽ አፈር ተደለቀ
ሁሉም ተሰናድቶ እልፍኙም አምሮበት
ከጽድቅ ገበያ የላኩት አሽከር ግን
አፍሮ ተመለሰ ዋጋ ተወዶበት።

ማዕዶት ያየሕ
28/02/2014
ከምሽቱ 05:50

@ethiopianpoem1
@yoyo556
2.0K viewsYoni Mak, 03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 06:47:22 ስሌት

ገደብን ሳስቀምጥ ለመጠበቅ ስሌት
ልኬታ ሰጥቼ እድሜ ሳሰፍርለት
ልቤ ሲያስቸግረኝ እስከመቼ ብሎ
መድረሻው ሲናፍቀዉ በመጠበቅ ዝሎ

እኔ ግን
የዛለዉን ልቤን ቁስሉን እያከምኩት
ነቃ በል አትቁሰል እልፍ ጠብቅ አልኩት
የማያልቅ እልፍ ቀን የማያልቅ ነገ ነው
ለልቤ የነገርኩት ሞት ገደብ አልባ ነው

ምክንያቱም
የሁልጊዜ ኑሮ የላይ ጅማሮ ነው
ሞት የሚለው ኬላ ስዉር መንገድ አለው

እናም
እናም ተዉ አላልኩት ነገን ይጠብቃል
ጊዜ ግን ሞኝ ነው እንዲሁ ይነጉዳል
ህመሙን ደብቆ ብዙ ይጓጓል ልቤ
አያልቅም እያልኩት በደንብ አሳስቤ
እድሜዬን ገፍትሮ ችግሬን ረግጦ
ማጣቴን ሳይሰማ ከይመጣል ፈጦ
ዛሬን ይጠብቃል ነገንም ጨምሮ
በቃል ኪዳኑ ላይ እልፍ ቀንን አስሮ

bira
@ethiopianpoem1
@yoyo556
1.9K viewsYoni Mak, 03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 06:47:00   ሀገረኛ ገላሽ
ፍቅርሽ ጠላ
መውደድሽ አንቡላ
ወየሁ ገላ
ያንቺ ገላ
ቲማቲም ነው እንዲሁ እሚበላ
ዓይንሽ ጥሬ ዜማ
አፍንጫሽ መንዙማ
መላክ የደረሰው ያዜመው በራማ
ነውና ያንቺማ
ወተወተው ውስጤን አስጮኸኝ በጉማ
  ጥርስሽ ቀንበር
   ከንፈሮችሽ ሞፈር
ልቤን ይገፉታል እንደ ግንቦት አፈር
   ምላስሽ ውራንታ
   አንደበትሽ ጎታ
እህል ልቤን
ጤፍ ስሜቴን
  ይለኩት ኣ!
  በልኬታ
ፀጉርሽ ገሳ
ክረምት የሚያስረሳ
ያድነኝ ኣ!
ከናፍቆትሽ ዝናብ
ከትውስታሽ አዜብ
  ከሚበሳ
  ከሚያሳሳ
አንገትሽ መሰላል
ትክሻሽ ሰዋስው
ሞኝ ልቤን ..
አንዴ ወዲያ አንዴ ወዲህ የሚያመላልሰው
  ወይ አንቺ ሰው !
አንቺ ሰው ነሽ አካሎችሽ ዕቃ
አይቻቸው
ዳስሻቸው
ገዝቻቸው መቼ ነው ማበቃ
  አላበቃም !
አነሳለሁ
እመለከታለሁ
እገዛለሁ
እያንዳንዱን በየተርታ
በፈገግታሽ መላክ
የሞት መላክ
ዕድሜየ እስኪገታ
ስለዚህ ጤናየ ...
   ደረትሽ የጤፍ ማሳ
   ጡትሽ ለጋ እንቦሳ
ደረትሽ ሲያበቅለኝ
ጡትሽ ነቃቀለኝ
መቼም ላልነሳ
ስለዚህ ጤናየ ...
   ብብትሽ የዕጣን ፅና
  ጐኖችሽ በገና
ብብትሽን ለማሽተት
ጐንሽን ለመስማት
    እመጣለሁ ...
ወደ መቅደስ ገላሽ ነጠላ ፍቅርሽን ልከናነብና
ስለዚህ ጤናየ ...
ወገብሽ የንብ ቀፎ
ዳሌሽ ዳቦ ድፎ
እመጣለሁ ...
ወደ ገለሻ ሀገር
ወደ ታቿ መንደር
  ማር ናፍቆቴን ልቆርጥ
   ለዝክር ውበትሽ  እማቀርበው ልመርጥ
ስለዚህ ጤናየ ...
እግሮችሽ የዕንጫት አልጋ
እጣቶችሽ ዕፁብ ፀጋ
  እንግዲህ ምን እላለሁ ምንስ ? ላውጋ
ሳቅሽን  እንዳላነሳ
ፍም ነው ያቃጥለኛል
ዝምታሽን እንዳላወሳ
መብረቅ ነው ያስደነግጠኛል
   ስለዚህ ጤናየ ...
ዝም
ፀጥ
ደሞ ርጭ ልበል
መቀኘት ካቃተኝ ለውበትሽ
ቁንጅናሽንም መመሰል ።
                  ንብ. 17/ 5 / 14

@ethiopianpoem1
@yoyo556
1.9K viewsYoni Mak, 03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 06:46:30 አጅሬዋ ስለመጡ
ህዝቡ ደስታውን አልቻለም
ወገብ ማሳረፊያ አተው
ሞልተዋል የቆሙም።
እንደ ልማዱ አስተዳዳሪው
ከመቀመጫቸው ብድግ አሉና
ወደ ጉዳያቸው ገቡ
የአክብሮት ሰላምታቸውን ሰጡና ...

"እንደምን ከረማችሁ
የተከበራችሁ ነዋሪዎቻችን
እናመሰግናለን ውድ
ጊዜያችሁን ስለሰጣችሁን።"አሉና
"አምና መንግስት ወተት
እንደሚልክ ቃሉን ሰቶ ነበረ
ግን ጥጆቹ ጡት
ገና አንለቅም ብለው ስለተቸገረ
እስኪለቁ እየጠበቀ
ወተቱን ሳይልከው ቀረ።"
ብለው ቀጠሉና
"ዛሬ ግን ህዝቤ እንኳን ደስ አላችሁ
የሚላስ ማር በቤታችሁ ላጣችሁ
ችግራችሁን አይቶ
ታዛዡ መንግስታችሁ
ቃል ገብቷል በቧንቧችሁ ሊልክላችሁ።"

ብለው ሲጨርሱ ካዳራሹ ያለው ህዝብ
በእልልታ ደባለቀው ምኑንም ሳያስብ።
በድንገት አቶ ካሴ
ብድግ አሉ እጅ ሳያወጡ
"ንቦቹስ ግን አያስቸግሯችሁም እንዴ?"
ብለው ተቀመጡ
በአሽሙር ከንፈራቸውን
ወደ ጎን እያሞጠሞጡ።
ሊቀ መንበሩም አሰብ አረጉና
አፀፋውን ሰጡ...

"ንቦቹ እንኳን ለእረፍት መቀሌ ስለገቡ
ቶሎ አይመለሱም
ለሱ እንኳን ብዙ አታስቡ።"

ብለው ሲናገሩ ሴቶቹ በእልልታ
ወጣቱ በፉጨት ህፃናት በዋይታ
አጨበጨቡላቸው ሁሉም በደስታ!!!
ከዚያም ቀጠሉና የሰፈሩ ጌታ...
"በሉ! እንደዚህ በደስታ እንደቦረቃችሁ
ቀፎ መግዣ የሚሆን
ያላችሁን እያዋጣችሁ
ወደ ቤታችሁ ሂዱ ለእኔ እየሰጣችሁ።"
ሲሉ ዋይታ እና እልልታው
በድጋሚ ተሰማ
ሁሉም ያለውን መዘዘ
ምንም ሳያቅማማ

ታዲያ እንዲህ ነው ወዳጄ
የመቀበያ ህግ
ለነገው ጥፋትህ መካሻ
ዛሬ ሰበብ ፈልግ!!!
ከማስተዋል ገዛኸኝ!!!(ማስቴ አፍሮ )


@ethiopianpoem1
@yoyo556
1.8K viewsYoni Mak, 03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ