2022-08-27 09:00:38
ለሊቱን የተደረገ ተጋድሎ
ዛሬ ሌሊት ሲደረግ በነበረው ውጊያ በቀዩ-ጋሪያ:በዋ:ቀመሌ:ሸወይ መንደር:ጀመዶ ቀበሌዎች እንደ አንበጣ ሰፍሮ የነበረው ወራሪ ሀይል እጅጉን በበረታው የወገን ጥምር ጦር ክንድ ተደቁሶ አድሯል:በመሆኑም ቆቦ ከተማን ለመታደግ የወገን ጦር ዛሬ ሌሊት ያደረገውን የፀረ-ማጥቃት ውጊያ በድል ቋጭቷል ማለት ይቻላል:ከዚህም በተጨማሪ መግለፅ በማልፈልገው አቅጣጫ የወገን ጦር ወራሪውን ለመቁረጥ ሙከራ እያደረገ ይገኛል።
ከቆቦ ከተማ በስተምዕራብ በኩል ወደ ግዳን ወረዳ አቅጣጫ - ሸወይ ፣ ገደባ ፣ ጎረጎሮ ፣ ፀበሉ ፣ ተኩለሽ እና በቀይ አፈር በሚባሉ የራያ ቆቦ ቀበሌወች ጦርነቱ ዛሬም እንደቀጠለ ነው ፤ በዚህ ግንባር የሃገር መከላከያ ሰራዊት እና የአማራ ልዩ ሃይል ለአካሉ ሳይሳሳ ለሀገሩ ያለውን ክብርና ለወገኑ ያለውን ፍቅር አሳይቷል።
በግዳን ወረዳ ግንባር - በወትወትና በድልድይ ከብዙ ተጋድሎ በኋላ ለጊዜውም ቢሆን የህውሃት ታጣቂዎች ወደ ኋላ አፈግፍገው ጥራሬን ተሻግረው ቦታ ይዘው ተቀምጠዋል ፤ ዛሬ ጧት በደረሰኝ መረጃ መሰረት መረዋ ላይ ሌሊቱን ብዙ ሃይል እንዳስገቡና ቦታ የመቀያየር ስራ ሰርተዋል ተብሏል ፤ በዚህ ግንባር ህዝቡ ጥቆማዎችን ለመንግስት ሃይሎች በማድረስ አጋርነቱን ያለመታከት ማሳየት ይኖርበታል !!!
በራያ አላማጣ~ዳዩ~ጋርጃለ ላይ ከወደ መቀለ ወደ ራያ ራዩማ እየገቡ የነበሩ የጁንታው ታጣቂወች ላይ አየር ሃይል ጥቃት አድርሷል።
#ሼር_አድርጉት
ቻናላችንን
JOIN በማድረግ
ወቅታዊ መረጃ ያግኙ
@ethiopianmerega
@ethiopianmerega
@ethiopianmerega
@ethiopianmerega
1.5K viewsKal Bekal, 06:00