2022-08-30 13:35:25
" ይህ ቀን ያልፋል ፤ ብንተሳሰብስ ? "
በዚህ በችግር ወቅት የተገኙበትን ማህበረስብ ከማገዝ ይልቅ የራሳቸውን ጥቅም ብቻ የሚያሯሩጡ አንዳንድ አካላት እጅግ በጣም አሳፋሪ ተግባር ላይ ተሰማርተዋል።
በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ባገረሸው ግጭት ሳቢያ በርካታ ሰዎች በተለይም ሴቶች እና እናቶች እንዲሁም አዛውንቶች ግጭት ያለባቸውን አካባቢዎች በመልቀቅ ሰላም እና ደህንነት ፍለጋ ለመሄድ እየተገደዱ ነው።
በአሁን ሰዓት ዳግም የጦርነት ቀጠና በሆኑት የአማራ ክልል አካባቢዎች የሚኖሩ ወገኖች ያለፈው ቁስላቸው፣ ህመማቸው ሳይሽር ዳግም ለከፍተኛ ለስቃይ ተዳርገዋል።
ህዝቡ ምን ያህል ችግር ላይ እና ሰቆቃ ላይ እንዳለ እየታወቀ ግን አንዳንድ ግለሰቦች የራሳቸውን ወገኖች በተሽከርካሪያቸው ከቦታ ወደ ቦታ ለመውሰድ እጅግ ከፍተኛ ገንዘብ እየተቀበሉ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
ያላቸው ገንዘቡን ይሰጣሉ የሌላቸው ግን በእግር ከከፍተኛ ድካም ጋር ሰላምን ፍለጋ ለመሄድ እየተገደዱ ነው።
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አካላት በትንሽ ኪሎ ሜትር እስከ 500 ብር ድረስ እና ከዛም በላይ እንደሚቀበሉ ለመስማት የቻልን ሲሆን በዚህ በችግር ወቅት እንዲህ የሚያደርጉ አካላት ቁጥጥር ሊደረግባቸው ከምንም በላይ ደግሞ ትልቁ ፈረጅ ህሊና ነውና ለህዝባቸው ቢያስቡ መልካም ነው።
ይህ ቀን ያልፋል ፤ የዛሬው ጭንቀት እና መከራ ወቅት ይቀየራል ፤ በዚህ ልክ መጨካከንና ህገወጥ ስራ መስራት አይገባም።
አሁን ላይ በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉት እና ግጭት ባለበት መስርመር ያሉ ከተሞች ገና ለገና ተፈናቃዮች መጡ በሚል ልክ እንዳለፈው ጊዜ ዋጋ ለመጨመር የሚሯሯጡ ነጋዴዎችም በመኖራቸው የሚመለከተው አካል ጥብቅ ቁጥጥር ሊያደርግ ይገባል።
2.0K viewsKal Bekal, 10:35