Get Mystery Box with random crypto!

ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ በርካታ ሰዎች ወደ አዲስአበባ እንዳይገቡ በፖሊስ መከልከላቸ | ኢ.ዜ.አ

ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ በርካታ ሰዎች ወደ አዲስአበባ እንዳይገቡ በፖሊስ መከልከላቸውን ገለጹ

ከአማራ ክልል በተለይም ከሰሜን ወሎና ደቡብ ወሎ በደብረ ብርሃን አቋርጠው ወደ አዲስ አበባ ለመግባት በአገር አቋራጭ ተሽከርካሪ የሚጓዙ ተሳፋሪዎች፣ ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡና ወደ መጡበት እንዲመለሱ መደረጋቸውን ተሳፋሪዎች ተናግረዋል፡፡

የሰሜን ሸዋ ዋና ከተማ ደብረ ብርሃንን አልፈው ከብዙ እንግልትና ፍተሻ በኋላ ወደ አዲስ አበባ ለመግባት የአዲስ አበባ የመጨረሻዋ መዳረሻ የሆነችው ለገዳዲ ከተማ ሲደርሱ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መታወቂያ የላችሁም ተብለው ወደ መጡበት እንዲመለሱ መደረጋቸውንና የሚደረገው ፍተሻም የተሳፋሪዎች ማንነት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን በርካታ ተሳፋሪዎች አስረድተዋል፡፡

የተሳፋሪዎችን ቅሬታ አስመልክቶ የሚመለከታቸውን አካላት ብናናግርም የሕወሓት ሠርጎ ገቦችን ለመያዝ ነው ከሚል ምክንያት ውጭ ዝርዝርና ግልጽ ምላሽ ማግኘት አልቻለም።
ተሳፋሪዎች ግን ማንነትን መሠረት ያደረገ ክልከላ ነው በማለት ገልፀዋል።

@Ethiopianewsagency (ኢዜአ)