Get Mystery Box with random crypto!

የ2012 የትምህርት ዘመን ወደ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት መግቢያ ነጥብ ይፋ ተደረገ | Ethiopian Students

የ2012 የትምህርት ዘመን ወደ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት መግቢያ ነጥብ ይፋ ተደረገ

******************

የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪውን የሰው ሃይል ስብጥርን በጠበቀ መልኩ በሀገሪቱ ያለውን የገበያ ፍላጎት መሰረት በማድረግ በየዓመቱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የቅበላ መስፈርት የሚያወጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ይህ ዓመት አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፍኖተ-ካርታ ጥናት ተጠናቆ ተግባራዊ እንዲሆን በርካታ የመሸጋገሪያ ተግባራት የሚከናወኑበት መሆኑን የገለፀው ኤጀንሲው ይህንን እና የገበያውን ፍላጎት አንዲሁም የሰው ኃይል አሰላለፍን ከግምጥ ውስጥ በማስገባት የ2012 የትምህርት ዘመን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የቅበላ መስፈርትን አውጥቷል፡፡

በዚሁ መሰረት፡-

በደረጃ 1 እና 2

10ኛ ክፍል ላጠናቀቁ

• ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 1.57 እና ከዚያ በታች
• ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች 1.43 እና ከዚያ በታች
• ሴት ታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 1.43 እና ከዚያ በታች
• ሴቶች ከታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢዎች 1.29 እና ከዚያ በታች
• ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 1.14 እና ከዚያ በታች

በደረጃ 3 እና 4

የ10ኛ ክፍል ላጠናቀቁ

• ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 1.71 እና ከዚያ በላይ
• ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች 1.57 እና ከዚያ በላይ
• ሴት ታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 1.57 እና ከዚያ በላይ
• ሴቶች ከታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢዎች 1.43 እና ከዚያ በላይ
• ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 1.29 እና ከዚያ በላይ

የ12ኛ ክፍል የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ለወሰዱ

• ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 134 እና ከዚያ በታች
• ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች 129 እና ከዚያ በታች
• ሴት ታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 129 እና ከዚያ በታች
• ሴቶች ከታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢዎች 124 እና ከዚያ በታች
• ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 99 እና ከዚያ በታች

በደረጃ 5

የ12ኛ ክፍል የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ለወሰዱ

• ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 135 እና ከዚያ በላይ
• ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች 130 እና ከዚያ በላይ
• ሴት ታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 130 እና ከዚያ በላይ
• ሴቶች ከታዳጊ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢዎች 125 እና ከዚያ በላይ
• ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 100 እና ከዚያ በላይ

በመቁረጫ ነጥቡ ላይ በደረጃ 5 ስር የተመለከተው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ለወሰዱ ተብሎ ቢቀመጥም 10ኛ ክፍል ተፈትነው 11ኛ ክፍል የሚያስገባ ነጥብ ያላቸው በተጠቀሰው ደረጃ ላይ መሰልጠን ይችላሉ ተብሏል፡፡


#source EBC
@Ethiopian_Students