" Filter ያልነካቸው " ኤልያስ ሽታኹን (የልደት ዳር ጨዋታ) ~ ~ ~ ~ ~ እንደክርቶስ ሐሙሴ ይመጣል:: "ይቺ ነገር ትለፈኝ "የምልበት :: ደመም ላብም ብቻዬን የማፈስበት:: የአትክልት ስፍራው ከኤርታሌ ብሶ የሚያቃጥለኝ ቀን አለኝ:: እስከዛው ትርካ .... አምዳምነቴ ልክ አልነበረውም:: እንዚህ ቀናቶች ለሰው የገረጡ ለኔ ግን ያጌጡ ናቸው:: አራት ኪሎ - የሰካራም ልጅ የተባልኩበት - የድሀ ልጅነቴ ስታይ የማስታውቅ እኔ - ጉልበተኛ ሀብታም ጎረቤት - ዉኃ የሚነጠባጠበት ቤት - የልጅነት ፀብ (አንዳንዶች አርጀተውም እኔን ለማሳፈር ይመዙልኛል)"እንዲህ ብለህ ነበር"ይላሉ - ፅዋ ማህበር (አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ) - ውድድር - ትልቅ ህልም ትንሽ አቅም - መጨረሻቸው ለሊት የሆኑ ወኮች - የክበብ ሽኩቻዎች - ጅንጅና ስልት ንድፎች - ያወቁትን ቤት መጥቶ ማውራት (ጥሩ ቦታ ነው የሚውለው እንዲባል) - ከእኩዮች ጋር አንድ አይነት ፋሽን መስራት.... ይሄ ሁሉ በህሊናና በልብ የቀሩ ማስታወሻዎች ናቸው:: ዛሬ ደሞ ለሰው ውብ ለራስ ግን ኮሽኳሻ ናቸው:: - ገላዬ ቆሽሾ በድንጋይ እህቴ ታላቅ እህቴ (ደርግ በሏት) ብረት ምጣድ ላይ እያጋጨች ፈተገችኝ:: "ማንን ለማሰድብ ነው" እያለች:: ጎረቤት አይሰማት ሰደበችኝ:: "ሰፈሩ እንደሆነ ቡዳ ነው" "እኔ እኮ..."ላስረዳ ስሞክር ወኃውን ሳየው ጠቁሯል:: እድፌ ጭቃ ያህል ወፍራም:: ዝም :: “ደሞ ባንተ እንሰድብ ወይ” (“ድው” ከብረት ምጣድ ጋር ታላትመኛለች) እልህ ዕንባ ነበራት:: አሁን ሳስባት ታሳዝነኛለች:: ምንበላው አልነበረንም ግን ስማችን አሳሰባት እና ጉልበቴ እስኪላጥ አሸችኝ:: ልክ እንደነዚህ ወዝም ደርዝም የሌለው የሚመስል እልፍ ቀን አለኝ @ethiopia2123 @ethiopia2123 257 viewsHáŷmî, 07:41