Get Mystery Box with random crypto!

በዛሬው እለት 20 ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው፡፡ 20 ዩኒቨርስቲዎች በተለያዩ የ | Ethio Fm 107.8

በዛሬው እለት 20 ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው፡፡

20 ዩኒቨርስቲዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በዛሬው እለት በማስመረቅ ላይ ይገኛሉ።

በዛሬው ዕለት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ከሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች መካከል አዲስ አበባ፣ ወለጋ፣ ደብረብርሃን፣ አርባምንጭ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ እና ሰመራ፣ ወልቂጤ እንዲሁም ኢንጅባራ ዩኒቨርስቲዎች ይገኙበታል፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያየ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን 8 ሺህ 642 ተማሪዎች በማስመረቅ ላይ ነው።

ከተመራቂዎቹ መካከል 5 ሺህ 121 በመጀመሪያ ዲግሪ ፣ 3 ሺህ 221 በሁለተኛ ዲግሪ እና 300 ተማሪዎች ደግሞ በሶስተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች መሆናቸው ተገልጿል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ላለፉት 73 ዓመታት በማስተማር እና በምርምር ስራ ላይ የቆዬ አንጋፋ የትምህርት ተቋም መሆኑ ይታወቃል።

ኢንጅባራ ዩኒቨርስቲ በምረቃ ስነስርአቱ ላይ ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው የክብር ዶክትሬት ዲግሪ መስጠቱንም አስታውቋል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም ለተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ሲል መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ሐምሌ 13ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube

https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos