Get Mystery Box with random crypto!

# ተጨማሪ መረጃዎች @ጸጋ በሲዳማ ብሔራዊ ክልል የፀጥታ ግብረ ሀይል በተደረገ የተቀናጀና በቴ | Ethio Fm 107.8

# ተጨማሪ መረጃዎች @ጸጋ


በሲዳማ ብሔራዊ ክልል የፀጥታ ግብረ ሀይል በተደረገ የተቀናጀና በቴክኖሎጂ የታገዘ ጠንካራራ ክትትል ወሪ/ት ፀጋ በላቸውን ከተጠርጣሪ ወንጀለኛ ማስመለጥ መቻሉ ተነግሯል፡፡


የፀጥታ ግብረ ሀይሉ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ የኃላመብራት ወ/ማሪያምን በቁጥጥር ስር ለማዋል ባደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ከትላንት 23/09/2015ዓ.ም ጀምሮ በምስራቅ ጉጂ ዞን ቦሬ ወረዳ ጀምሮ ተጠርጣሪ ወንጀለኛውን በመከታተልና መፈናፈኛ በማሳጣት በዛሬው እለት በሻፋሞ ወረዳ ሹሮ ቀበሌ ወሪ/ት ፀጋ በላቸውን ከግለሰቡ ማስጣል ተችሏል፡፡


ግለሰቡ ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ ወደጫካ የገባ ቢሆንም የፀጥታ ግብረ ሀይሉ ያልተቋረጠ ክትትል በማድረግ ተጠርጣር ወንጀለኛን በመከታተል ላይ ይገኛል፡፡


ለዚህ ስምሪት መሳካት ከፍተኛ አስተወጽኦ ላበረከቱ ለብሔራዊ መረጃ ደህንነት፣ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል፣ ለሻፋሞ ወረዳ አስተዳደርና የህብረተሰብ ክፍል የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮና የፀጥታ ግብረ ሀይል ልባዊ ምስጋና ያቀርባል፡፡

ተጠርጣሪ ወንጀለኛውንም በቁጥጥር ስር በማዋል ለህግ ለማቅረብ በጫካው ውስጥ አሰሳ እየተካሄደ ሲሆን የሚገኙ ውጤቶችን ለመላው የሀገራችንና የክልላችን ህዝቦች የምናሳውቅ ይሆናል ብሏል ፡፡

በሔኖክ ወ/ገብርኤል

ግንቦት 24 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos