Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Anti Corona

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioanticorona — Ethio Anti Corona E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioanticorona — Ethio Anti Corona
የሰርጥ አድራሻ: @ethioanticorona
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 294
የሰርጥ መግለጫ

🏮Ethio Anti Corona 🏮
#EAC
ወዳጅ ዘመድዎን ወደዚህ ቻነል እንዲቀላቀሉ ያድርጉ!
ስለ ኮሮና ቫይረስ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፣ መከላከያ መንገዶች እና መረጃዎች የሚቀርቡበት ቻነል!
#COVID19
#Ethiopia
@EthioAntiCorona

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2020-04-13 09:12:48
የአፍሪካ ህብረት ቻይና በሚኖሩ አፍሪካውያን ላይ የሚደርሰው ጥቃት እንዳሳሰበው ገለፀ

የአፍሪካ ህብረት የቻይና ባለስልጣናት በቻይናዋ ከተማ ጉዋንጉዙ የሚኖሩ አፍሪካውያን የሚደርስባቸውን ጥቃትና መድልዎ እንዲያስቆሙ ተናገረ።

በቅርቡ በጉዋንግዙ የሚኖሩ አፍሪካውያን ኮሮና ቫይረስን ያዛምታሉ በሚል ከሆቴላቸው እንዲሁም ከጋራ መኖሪያ ቤቶቻቸው እንዲወጡ ተደርገዋል።

የአፍሪካ ህብረት ከሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ ማሃማት በአፍሪካ ህብረት የቻይና አምባሳደርን አስጠርተው በአፍሪካውያን ላይ እየደረሰ ያለው ዛቻና ጥቃት እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል።

ሊቀ መንበሩ አክለውም በቻይና የሚገኙ አፍሪካውያን ዲፕሎማቶች የቻይና ባለስልጣናት ጋር ውይይት እያደረጉ ነው ብለዋል።

የናይጄሪያ፣ ኬንያና ሴራሊዮን ዜግነት ያላቸው አፍሪካውያን ከሚኖሩበት የጉዋንጉዙ ከተማ ሆቴሎችና የጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲወጡ ተደርገው ውጭ እንዳሉ አሳውቀዋል።

አንዳንዶችም ምንም እንኳን ተመርምረው ውጤታቸው ከኮሮና ነፃ መሆናቸውን ቢያሳይም በአስገዳጅ ሁኔታ ለይቶ ማቆያ ውስጥ እንዲገቡ መደረጋቸውን ገልፀዋል።

የቻይና ባለስልጣናት በበኩላቸው 'ሊትል አፍሪካ' ተብሎ በሚጠራው ሰፈር በቫይረሱ የተያዙ ናይጄሪያውያን የአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ህጉን በመተላለፋቸው፤ ይሄም ሁኔታ በህዝቡ ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል ብለዋል።

ምንጭ ቢቢሲ
2.0K viewsedited  06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-04-12 19:08:56
በዚህ መልኩ የሚደረግ ምርመራ ምናልባት ቫይረሱ ካለበት አካል አንስቶ ወደሌላው ሰው ግንባር ማሰራጫ መንገድ እንዳይሆን የጥንቃቄ ጥቆማችንን እናስተላልፋለን።
1.8K viewsedited  16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-04-11 19:51:40 በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተከለከሉ ተግባራት

1• ማንኛውም ሐይማኖታዊ፣ ፖለቲካዊ ስብሰባዎች፣ከአራት ሰው በላይ የሚገኝባቸው እድርን፣ደቦን፣እቁብንናሌሎች ባህላዊ ስብሰባዎችን ማካሄድ ተከልክሏል። ነገር ግን ቀብርና ሌሎች አስፈላጊ ሁኔታዎች ሲኖሩ እየታዩ ሊፈቀዱይችላሉ።

2• በመጨባበጥ ሠላምታ መለዋወጥ ተከልክሏል።

3• ተማሪዎችና መምህራን በአካል መገናኘት ተከልክሏል።

4• ታራሚዎችተገቢው ጥንቃቄ ተደርጎ ከጠበቆቻቸው የሚገናኙ ሲሆን፤ ታራሚዎችን መጠየቅ ተከልክሏል።

5• በፖሊስ ቁጥጥር ስር ላሉ እስረኞች ስንቅ ከማቀበልውጪ መገናኘትተከልክሏል።

6• የአገሪቱ ድንበር ከካርጎ፣ከደረቅና ፈሳሽ የጭነት ተሽከርካሪዎች ውጪ ሌሎች ለሌሎች ዝግ ሆኗል።

7• የቤት ተከራዮችን ማስለቀቅ ወይም ኪራይ መጨመር ተከልክሏል።

8• ሠራተኞችን መቀነስና የሥራ ቅጥር ውልን ማቋረጥ ተከልክሏል።

9• ስፖርታዊ ጨዋታዎችና የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎች ክልከላ ተጥሎባቸዋል።

10• የአገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎች ካላቸው መቀመጫ ከ50 በመቶ በላይ ተሳፋሪ መጫን ተከልክሏል።

11.ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ሃሰተኛ መረጃዎችን ማሰራጨት፣ማጋነን እና ማቃለል የተከለከለ ነው

12ወረርሽኙን ለመከላከል መንግስት ሊጠቀምባቸው የፈለጋቸውን ቤቶች፣ሆቴሎች፣መኪኖች እና ሌሎች አጋዥ ነገሮችን ባለቤቶቹ እንዲሰጡ በተጠየቁበት ሰዓት የመተባበር ግዴታ አለባቸው

13 ህዝብ በብዛት የሚገለገልባቸው. ቦታዎች እንደ ባንክ፣የንግድ ቦታ እና የመሳሰሉ ቦታዎች ርቀትን ሳይጠብቁ ቢያንስ 2ሜትር ሳይርቁ መቀመጥም ሆነ መቆም የተከለከለ ነው
930 views16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-04-11 18:15:16
የኮሮና ቫይረስ #ኮቪድ -19

ወቅታዊ ሁኔታ
794 viewsedited  15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-04-10 13:22:30 በኢትዮጵያ ተጨማሪ 9 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው
አምስቱ ከዱባይ የመጡ ሲሆን ሁለቱ ከቱርክ፣አንዷ ከእንግሊዝ ሌላው ደግሞ ከአሜሪካ የመጡ ናቸው!
923 views10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-04-10 12:07:01
Ministry of Health,Ethiopia

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአብላጫ ድምጽ አጸደቀ።
________
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመቆጣጠር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተግባራዊ እንዲደረግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።

ምክር ቤቱም ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባው የኮቪድ -19 ስርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአንድ ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።

#Corona_Virus
#COVID-19

#EAC
@EthioAntiCorona
1.9K viewsedited  09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-04-09 09:50:28
ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ መረጃ የሚሰጥ የዋትስአፕ ቻት ቦት ሥራ ላይ ዋለ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ መረጃ የሚሰጥ የዋትስአፕ ቻት ቦት ሥራ ላይ አዋለ።

የዋትስአፕ ቻት ቦት አላማ ለዜጎች ትክክለኛውን መረጃ ለማቅረብ ከህዝብ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንዲኖረው ሲሆን፥ ይህ የኢትዮጵያን ለቫይረሱ ያላትን ብሄራዊ ምላሽ በመደገፍ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።

ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ መረጃ የሚሰጥ የዋትስአፕ ቻት ቦት ሥራ ላይ መዋሉን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

[Govt of Ethiopia Covid-19] የሚያል ስያሜ ያለው ቻት ቦት ለዜጎች ትክክለኛ የጤና መረጃን ለማድረስ በዋትስአፕ ላይ መቅረቡ ነው መረጃው የገለጸው።

ለአጠቃቀሙ ሁለት አማራጮች የተዘጋጁ ሲሆን፥ አንደኛው በቀጥታ የሚከተለውን ሊንክ በመጫን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ QR ኮድ ስካን በማድረግ ነው።

https://api.whatsapp.com/send ...


#Corona_Virus
#COVID-19

#EAC
@EthioAntiCorona
2.4K viewsedited  06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-04-08 20:20:48
የCOVID-19 ወቅታዊ ሁኔታ!

#Corona_Virus
#COVID-19

#EAC
@EthioAntiCorona
788 viewsedited  17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-04-07 17:03:06
በኢትዮጵያ አንድ የ9 ወር ህጻንን ጨምሮ ተጨማሪ ስምንት ሰዎች በኮሮናቫይረስ ተያዙ

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 264 ሰዎች ውስጥ 8 ሰዎች በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ።

በቫይረሱ ከተያዙት ሰዎች መካከል አንድ የዘጠኝ ወር ህጻን የተያዘ ሲሆን እናቱም ቫይረሱ ተገኝቶባታል።


የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በ24 ሰዓታት ውስጥ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች መካካል አንዱ ኤርትራዊ ሲሆን ቀሪዎቹ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው።

ይህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 52 አድርሶታል ነው ያሉት።

በበሽታው መያዛቸው ከተረጋገጠ ስምንቱ ሰዎች መካከል አምስቱ ከዱባይ የመጡና በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩ ናቸው።

ከእነዚህም ውስጥ አንድ የዘጠኝ ወር ህጻንና ወላጅ እናቱ ይገኙበታል።

አንድ የ25 ዓመት ሴት ኢትዮጵያዊት ከታይላንድ መጥታ በለይቶ ማቆያ ክትትል ስታደርግ የነበረች ሲሆን፤ አንድ የ19 ዓመት ኢትዮጵያዊ የውጭ አገር ጉዞ ታሪክ የሌለው ሲሆን የንክኪ ሁኔታውም በመጣራት ላይ ይገኛል ብለዋል።

ሌላኛዋ የ30 ዓመት ሴት ኤርትራዊት ስትሆን ከእንግሊዝ ለንደን መጥታ በአዲስ አበባ በለይቶ ማቆያ ክትትል እያደረገች የምትገኝ ናት።

በአዲስ አበባ እና በሌሎች የክልል ከተሞች የኮሮናቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ አቅም እየጨመረ መጣቱንም ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መካከል አንድ ግለሰብ በጽኑ ህሙማን ማቆያ ይገኛሉ።

አራቱ ያገገሙ ሲሆን፤ ሁለቱ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።

ሌላ ሁለት ግለሰቦች ደግሞ ወደ ሀገራቸው ተሸኝተዋል።
962 viewsedited  14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ