የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች:
294
የሰርጥ መግለጫ
🏮Ethio Anti Corona 🏮
#EAC
ወዳጅ ዘመድዎን ወደዚህ ቻነል እንዲቀላቀሉ ያድርጉ!
ስለ ኮሮና ቫይረስ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፣ መከላከያ መንገዶች እና መረጃዎች የሚቀርቡበት ቻነል!
#COVID19
#Ethiopia
@EthioAntiCorona
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
2
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2020-06-04 16:50:07
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 150 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 5,141 የላብራቶሪ ምርመራ አንድ መቶ ሃምሳ (150) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 1,636 ደርሷል፡፡
ቫይረሱ የተገኘባቸው 94 ወንድ እና 56 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ3 እስከ 72 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 147 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ሶስቱ (3) የውጭ ዜጎች ናቸው።
ቫይረሱ የተገኘባቸው 123 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 1 ሰው ከአፋር ክልል፣ 2 ሰዎች ከትግራይ ክልል፣ 3 ሰዎች ከደቡብ ክልል፣ 2 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣ 13 ሰዎች ከአማራ ክልል እና 6 ሰዎች ከሶማሌ ክልል ናቸው።
ተጨማሪ መረጃ ፦
በትላንትናው አራት (4) ሰዎች ከአዲስ አበባ ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 250 ደርሰዋል።
904 views13:50
2020-05-28 08:12:13
በአዲስ አበባ ከተማ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መያዛቸው የተረጋገጠ 458 ሰዎች ክፍለ ከተማ እንደሚከተለው ቀርቧል ፦
• ልደታ - 122 ሰዎች
• አዲስ ከተማ - 79 ሰዎች
• ቦሌ - 56 ሰዎች
• ጉለሌ - 40 ሰዎች
• ኮልፌ ቀራኒዮ - 40 ሰዎች
• ንፋስ ስልክ ላፍቶ - 27 ሰዎች
• የካ - 26 ሰዎች
• አራዳ - 21 ሰዎች
• ቂርቆስ - 16 ሰዎች
• አቃቂ ቃሊት - 10 ሰዎች
* አድራሻቸው በመጣራት ላይ ያለ - 21 ሰዎች
999 views05:12
2020-05-07 15:52:39
በኢትዮጵያ 25 ተጨማሪ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው!
19የሚሆኑት ከበሽተኛ ሰው ጋር ምንም ንክኪ እና የውጪ ጉዞም ያልነበራቸው ናቸው!
የቁጥሩ መጨመር በጣም አስደንጋጭ እየሆነ ነው!
አላህ ይሁነን!!
2.5K views12:52
2020-05-06 13:17:06
17ተጨማሪ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው!
7ቱ ከጅቡቲ የተመለሱ፣6ቱ ከሶማሊያ የተመለሱ እና 4ቱ ደግሞ ከአዲስ አበባ ናቸው::
ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 93 ደርሷል::
2.4K views10:17
2020-04-28 14:05:46
Report #46
የኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ መግለጫ
Status update on
# COVID19Ethiopia
እርማት:- ከታች በተገለጸው መግለጫ ላይ 4 አመት እድሜ ተብሎ የተገለጸው 42 አመት በሚል ማስተከከያ እንዲደረግበት ከይቅርታ ጋር እንጠይቃለን።
1.3K views11:05
2020-04-20 14:42:22
Ministry Of Health,Ethiopia\
የኢትዮጲያ ጤና ሚኒስቴር
Report #38
የኮሮና ቫይረስ ( # ኮቪድ -19) ወቅታዊ ሁኔታ
2.4K viewsedited 11:42
2020-04-17 19:50:01
ብረት ነክ እቃዎችን ከነኩ እጆትን ይታጠቡ !
ማንኛውም ብረት ነክ ዕቃዎችን ከነካን ቢያንስ ለ 40 ሰከንድ እጃችንን በሳሙና እና በውሃ መታጠብ ያስፈልጋል።
የጤና ጥበቃ ሚኒስትር
2.5K viewsedited 16:50
2020-04-15 14:20:00
ቻይና የህክምና ባሉሙያዎችን ወደ ኢትዮጵያ ልትልክ ነው
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የምታደርገው ጥረት የሚደግፉ የህክምና ባለሙያዎችን ቻይና ወደ ኢትዮጵያ ልትልክ ነው።
ቻይና ከኢትዮጵያ በተጨማሪም የህክምና ባለሙያዎችን ወደ ቡርኪና ፋሶ እንደምትልክ ነው የተገለፀው።
እነዚህ የህክምና ባለሙያዎች ልምዳቸውን ያጋራሉ እንዲሁም የኮሮና ቫይረስን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የሚያስችሉ መመሪያዎችን እና ቴክኒካል ምክሮችን ለጤና ባለሙያዎች እና ለህክምና ተቋማት ያካፍላሉ ተብሏል።
ቻይና ከአፍሪካ ጋር ጠንካራ ግንኙነት እንዳላት የገለፁት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዝሆ ሊጂዓን በአፍሪካ ቫይረሱን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እየተከናወነ ያለውን ስራ ሀገራቸው እንደምትደግፍ ገልፀዋል።
በአፍሪካ ሀገራት ያለውን ሁኔታ በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን ያስታወቀችው ቻይና ቫይረሱን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የሚያስችሉ መሳሪያዎችን ማቅረቧን ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል።
2.2K viewsedited 11:20
2020-04-13 19:43:07
ሙቀት ሲለኩ ተገቢውን ርቀት ይጠብቁ!
ከ 3 እስከ 5 ሴንቲ ሜትር ይራቁ!
2.3K viewsedited 16:43
2020-04-13 11:53:21
በቻይና ከውጭ ሃገራት የገቡ 108 በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ተገኙ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቻይና ከውጭ ሃገራት የገቡ አዳዲስ 108 በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ተገኙ።
የሃገሪቱ የጤና ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ከሰሞኑ ከተለያዩ ሃገራት የገቡ ሰዎች ላይ በተደረገ ልየታና ክትትል 108 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ይህ ቁጥር ቻይና የኮሮና ቫይረስን መቆጣጠሯን ከገለጸች በኋላ በሳምንት ውስጥ የተመዘገበ ከፍተኛው መሆኑም ነው የተነገረው።
በቻይና 83 ሺህ135 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 3 ሺህ 219ኙ ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል።
77 ሺህ 956 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
2.1K viewsedited 08:53