Get Mystery Box with random crypto!

#Report በዓለም ኣቀፍ ደረጃ የኮቪድ-19 የ24 ሰዓታት ሪፖርት፦ - በመላው ዓለም 14,99 | ኢትዮ መረጃ - NEWS

#Report

በዓለም ኣቀፍ ደረጃ የኮቪድ-19 የ24 ሰዓታት ሪፖርት፦

- በመላው ዓለም 14,996 ሰዎች በ24 ሰዓት ውስጥ በኮቪድ-19 ሳቢያ ሞተዋል፡ 589,158 ሰዎች በቫይረሱ መያቸው ተረጋግጧል።

- አሜሪካ ባለፉት 24 ሰዓት የ3,652 ዜጎቿን ህይወት ስታጣ፤ 169,033 ሰዎች ለቫይረሱ መጋለጣቸው ተረጋግጧል።

- በዩናይትድ ኪንግደም ባለፉት 24 ሰዓት 1,245 ሰዎች ሲሞቱ፤ 29,079 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ተረጋግጧል።

- ብራዚል 1,099 ዜጎቿን በ24 ሰዓት ውስጥ በኮቪድ-19 ስታጣ ፤ 58,691 ዜጎቿ በቫይረሱ ተይዘዋል።

- ሜክሲኮ 1,506 ዜጎቿ ባለፉት 24 ሰዓት ሞተዋል፤ አጠቃላይ በሀገሪቱ የተመዘገበው የሟቾች ቁጥር 155,145 ደርሷል።

- በኮቪድ-19 የሚሞቱባት ዜጎች ቁጥር እየጨመረ በመጣው ጀርመን ባለፉት 24 ሰዓት 832 ሰዎች ሞተዋል።

- ሩስያ 534፣ ፈረንሳይ 510 ፣ ስፔን 513 ፣ ጣልያን 477 ዜጎቻቸው በ24 ሰዓት ውስጥ ካጡ ሀገራት መካከል ናቸው።

- በደቡብ አፍሪካ የሟቾች ቁጥር በእጅጉ ጨምሯል፤ባለፉት 24 ሰዓት የተጨማሪ 528 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል። ባለፉት 5 ቀናት ብቻ 2,759 ሰዎች ሞተዋል።

- በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ሪፖርት እንደሚያስረዳን 102,635,253 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል፥ የ2,216,418 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ 74,329,277 ሰዎች አገግመዋል።

ውድ የቲክቫህ አባላት ከወረርሽኙ እራሳችሁን፣ ቤተሰባችሁን ትጠብቁ ዘንድ አደራ እንላለን ፤ በሽታው ሳናውቀው በርካቶችን ከጎናችን እንዳያሳጣን እንጠንቀቅ ! ዘውትር የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ(ማስክ) ማድረጎን፣ የእጆን ንፅህና መጠበቆን፣በየትኛውም ቦታ ርቀቶን መጠበቆን፣ሰዎች በብዛት ከሚሰበሰቡበት ቦታ መራቆን አይዘንጉ።

መረጃው የቲክቫህ ነው

@ethio_mereja_news