Get Mystery Box with random crypto!

በጎደሬ ወረዳ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት አንድ የፖሊስ አዛዥ ተገደለ ከደቡብ  | ኢትዮ መረጃ - NEWS

በጎደሬ ወረዳ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት አንድ የፖሊስ አዛዥ ተገደለ

ከደቡብ  ምዕራብ ክልል ሚዛን ከተማ ወደ ጋምቤላ ክልል ማጃንግ ብሔረሰብ ዞን ጎደሬ ወረዳ ሜጢ ከተማ በመጓዝ ላይ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ባደረሱት  ጥቃት የአንድ ፖሊስ አዛዥ ተገድሏል። በጥቃቱ አንድ የፖሊስ  አባል ላይ ጉዳት መድረሱን በጋምቤላ ክልል የጎደሬ ወረዳ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዳኜ ወርቅነህ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

ጥቃቱ የተፈፀመው በደቡብ ምዕራብ ክልል የኪ ወረዳ  ልዩ ስሙ ባያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ  ነው። ጥቃቱ ሰኔ 4 ቀን 2015 ዓ.ም  ከምሽቱ 1 ሰዓት 30 ደቂቃ አካባቢ ተፈፅሟል።

ይህ ግድያ የተፈጸመው የፖሊስ  አባላቱ ከደቡብ ምዕራብ ክልል ሚዛን ከተማ ስልጠናቸውን ጨርሰው ወደ ጎደሬ ወረዳ ሜጢ ከተማ በመመለስ ላይ እያሉ ነው ብለዋል።ጥቃቱንም የጦር መሳሪያ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ፈፅመውታል።

በጥቃቱ የማጃንግ ብሔረሰብ ዞን የጎደሬ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ አብዮት ሮኬት ህይወታቸው አልፏል። በሌላ አንድ የፖሊስ አባል ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ተከትሎ በቴፒ ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገለት ይገኛል ሲሉ አቶ ዳኜ ወርቅነህ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

ድርጊቱን በፅኑ የሚያወግዝ መሆኑን እና አጥፊዎቹም ለህግ እንዲቀርቡ ከፍትህ አካላትና ከሚመለከታቸው ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገልፀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news