Get Mystery Box with random crypto!

'በሌላ አርቲስት የስነ ጥበብ ተቃውሞ የተነሳ ዮናስ ብርሃነ መዋን ማሰር እና በዋስ የመፈታት መብት | ኢትዮ መረጃ - NEWS

"በሌላ አርቲስት የስነ ጥበብ ተቃውሞ የተነሳ ዮናስ ብርሃነ መዋን ማሰር እና በዋስ የመፈታት መብት መከልከል ሕግን የጣሰ እና ተቀባይነት የሌለው ነው።" የኢሰመኮ ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ

በሌላ አርቲስት የስነ ጥበብ ተቃውሞ የተነሳ ዮናስ ብርሃነ መዋን ማሰር እና በዋስ የመፈታት መብት መከልከል ሕግን የጣሰ እና ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ ገለጹ።

ኮሚሽነር ዳንኤል በፌስቡክ ድረ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ ባሳፍነው አርብ ሰኔ 2/2015 በፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለው የፊልም አዘጋጅ ዮናስ ብርሃነ መዋ ከእስር እንዲለቀቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም፤ በሌላ አርቲስት የስነ ጥበብ ተቃውሞ የተነሳ ዮናስ ብርሃነ መዋን ማሰር እና በዋስ የመፈታት መብት መከልከል ሕግን የጣሰ እና ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ገልጸዋል። የአርቲስቷ ስነ ጥበብ ተግባር በነፃነት የመናገር መብት አካል እንደሆነና ዮናስ ብርሃነ መዋ በፍጥነት ከእስር ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቅ ሲሉም ጠይቀዋል።

የ"ጉማ አዋርድ" አዘጋጅ ዮናስ ብርሃነ አርብ ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ከተካሄደው የሽልማት ሥነ ስርዓት በኋላ በመንግሥት የጸጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋሉ ይታወሳል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news