ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ለሚያስገነቡት አዲስ ቤተመንግሥት ተጨማሪ ሦስት ተቋራጮች መቅጠራቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች። የ"ጫካ" ፕሮጀክት አጠቃላይ ወጪው 49 ቢሊዮን ብር እንደሚደርስ ሲገለጽ የቆየ ሲኾን፣ የምዕራባዊያን ዲፕሎማቲክ ምንጮች ግን ወጪው 850 ቢሊዮን ብር ሊደርስ እንደሚችል በመናገር ላይ ናቸው። ፕሮጀክቱ በ503 ሔክታር ላይ የቅንጡ መኖሪያና መዝናኛ መንደሮችንና ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቆች ግንባታ ያካተተ ሲኾን፣ ግንባታው የሚካሄደው በየካ ክፍለ ከተማ የካ ተራራ ግርጌ ነው። የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን እስካኹን የ29 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታ አካሂዷል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news 12.4K views16:18