Get Mystery Box with random crypto!

​​. ​ ◉●◦ አለሜ ነሽ ◦◉ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ | ኢትዮ-ልቦለድ & ❤️❤️📚

​​. ​ ◉●◦ አለሜ ነሽ ◦◉

ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ

▣ አንብበው ሲጨርሱ ሼር ያርጉ ▣

#ክፍል_2


ደራሲ ቤዛዊት ፋንታዬ የሽዋ ልጅ



... የዚህችን ሴት ምንነት ለመግለፅ ምን ይሆን የከበደው..? የሚለውን ጥያቄ ሲጮኽ
የሰሙት ሰዎች በውስጣቸው ያለ ማቋረጥ እያሰቡት ነው ። አለሙ ማን ናት
ህይወቱስ ማን ናት?
ድቅደቁ ምሽት ተገፎ ወደ መነጋጋቱ ወስዶታል ። ብርሀን እየመጣ ነው ።
ጨለማው ለውጦ ፀሀይ ቦታዉን ተረክባለች። ኮማ ውስጥ ያለችው
ሴት ቀኑን እና ለሊቱን ያለ ልዩነት በስቃይ ውስጥ ነች።
ማታ ሆስፒታሉን ሲቀውጠው ያደረው ያ ለግላጋ ስውም በእንባ እና በእንቅልፍ
አብጦ አይኑን እያሻሽ ተነስቶ ኮማ ውስጥ ወዳለችው ሴት አመራ ።
በጉጉት እና በናፍቆት ሲከንፍ ሄዶ አያት ። ምንም የተነቃነቀም ሆነ የተለወጠ ነገር
የለም ። ዛሬ ከትላንት ለእሱ የተለየው መሽቶ መንጋቱ ብቻም አይደለም። የሚሳሳላት ሴት በህይወት መኖሯም ተመስገን አስኝቶታል ።
ሰላም ስላሳደራት...ሰላም እንዲያውላት እና እንዲያኖራት ወደ ቤተ ክርስቲያን ፈጣሪዉን ሊያመስገን ፤ ሊማፀን ሄደ ። በሃሳብ ሩቅ ስለነጎደ ረዥሙ መንገድ አልታወቀውም ። በስተመጨርሻ
እራሱን ቤተ ክርስቲያኑ ደጃፍ ላይ አገኘዉ። ሰማይ እና ምድርን..ሙት
እና በህይወት ያሉትን ነገሮችን በሙሉ የማንቀሳቀስ እና የማዘዝ መብት ላለው
ፈጣሪ ስላምታውን አቀርበ ። ወደ ግቢው ዘልቆ ገባና አንድ ድንጋይ
ላይ ቁጭ አለ።

ግማሹ ቁሞ ሌላው ተቀምጦ ከፊሉ ደግሞ ተንበርክኮ ምልጃውን ያደርሳል ። በጉልበቱ ተንበርክኮ አለሙ የሆነችውን.. እስትንፋሱ የሆነችውን ሴት እንዳይወስድበት
ተማፀነው ። ቀጥሎ ዝም ብሎ ቆየ ። ከራሱ ጋርም እንዲ ሲል ሙግት ገጠመ
"ቆይ ፈጣሪ ቂም ያዉቃል እንዴ..? ለምንድነው አዳምና ሄዋንን ይቅር ያላላቸው። አይ..አይ ለነገሩ
አታድርጉ የተባለውን ነገር ስላደረጉ ነው ። ቆይ ታድያ ፈጣሪ ሀጢያት እንደሚሰሩ
ካወቀ ለምን አላስቆማቸውም..? ለነገሩ ማሰቢያ አእምሮ ሰጥቷቸዋል.. ማስብ የእነሱ ድርሻ ነው ። ልንሞት ነገርስ ለምን ተፈጠርን..? ምን ሆኜ ነው ...ፈጣሪ
የፈጠርንኮ ለመግደል ብሎ አይደለም ። እሱማ ያረገው ነገር ቢኖር ነፃነትን
ከእውቀት ጋር መስጠት ነው ። ፈጣሪን ከምወቅስ አታድርጉ ተብሎ ላረግነው እኛ
ለምን ክስ አላቀርብም..? ምን እየሆንኩኝ ነዉ!! ፈጣሪ ፍቅር ነው ።
ጥላቻን እንድናውቅ ያረገን የፍቅርን ሀያልነት ሊያሳየን ስለፈለገ ነው ። አዳም
ብቻውን ቆዝሞ ከራሱ ጋር ያወጋል ። ስለማንም ግድ አልሰጠውም ። የእሱ ሄዋን አሁን አጠገቡ የለችም ።
ወደ ራሱ ተመለሰ በሀዘኑ ምክንያት የተንጨበረረ ፀጉሩን እና ፂሙን በተራ እየዳበሰ ተንጠራርቶ ተነሳ ። ወደ ሀኪም ቤት ተመለሰ።

በጣም ርቦታል መብላት ፍልጓል። ያለ እሷ መብላቱን ሊለምደው አልቻለም ።
ከትላንት ጀምሮ ምግብ በአፉ አልዞረም ። ለመብላት በማስብ ወደ ሀኪም ቤቱ ካፌ ሄደና ተቀመጠ ።

ቀጫጫ ረዘም ያለ አስተናጋጅ ቀልጠፍ ብሎ " ምን ይምጣ ወንድሜ " አለው
"እእ ቀለል ያለ ቁርስ ባንተ ምርጫ ይሁንልኝ" አለው ።
አስተናጋጁም ሲከንፍ ሄዶ ምርጥ ዱለት ከውሀ ጋር አመጣለትና መልካም ምግብ ብሎት ሄደ ። እጁን ታጥቦ ዱለቱን
በፍጥነት በልቶ ጨርሰ ። የራሱን ሆድም በጣም ታዘበው ። "ለካስ ስጋና ነብስ የተለያዩ ናቸው ።" አለ በውስጡ
"እሷ ተኝታ እኔ ግን በላሁ" አለ
ምግብ መቅመሱ በትንሹ ያረጋጋው ይመስላል ። ከበላ በኋላ አረፍ ማለት ቢፈልግም አልቻለም ። ልቡ እና ሀሳቡ ሄዋኑ ጋር ነው ። እርሷ ጋር ሲደርስ ብቻዋን አልነበርችም ። አጭሯ ነርስም
ነበረች ። በውስጡ "ይህቺ ነርስ ቀንና ለሊት ነው እንዴ የምትሰራው" ሲል እያሰበ ተጠጋት ።
በስስ ፈገግታ ስላም ተባባሉ።
ነርሷ አተኩራ እያየችው " ትላንት ግን" አለችና ፀጥ አለች
"ትላንት ምን..?" አላት
"አይይይ በጣም ጮኸክ በስላም ነው..?" አለችው
የትላንቱ ትዕይንት በአይነ ህሊናዋ እየታያት ።
"ልብሽን አሞሽ ወይም ልቡን የታመመ ሰው አጋጥሞሽ ያዉቃል ..?" አላት
" ዉይ አዎ !! ይገርምሃል ጎረቤቴ ልቡን አሞት ነበር ። ማለቴ የልብ ድካም
አለበትና በቃ ሊሞት ለጥቂት ነው የተረፈው " አለችው ።
አዳም ትንሽ ሊስቅም
ቃጣው ። ሌላ ጊዜ ቢሆን በደንብ ይስቅ ነበር ። አሁን ግን የሚስቅበት አንደበት የለውም ።
ፈገግ ብሎ እያያት
" እሱኛውን የልብ ህመም አደለም ያልኩሽ ። በፍቅር ምክንያት ሰለሚታመም
ልብ ነው የጠየቅኩሽ ። ልክ እንደኔ በፍቅር መስቃየት የሚወዱትን.. የሚያፈቅሩትን ስው በቅርብ በአይን እያዩት በእጅ የማይነኩትን ነዉ የምልሽ..የሚወዱትን ሰው ትንፋሽ
ካጠገቡ ሳትርቂም እስትንፋሱን አለመስማት... ድምፁን መራብ በጣም ያማል ። ቅስምን ይስብራል ። ይህንን ህመም . ..
ይህንን ስቃይ ነው ያልኩሽ" አላት
አሳዘናት... ያላትን ነገር
ተረደተዋለች። እጇን ወደእሱ ሽቅብ እየዘረጋች "እንተዋወቅ ዲና እባላለው... ቅር ካላለህ የሁለታችሁንም ስም ብትነግርኝ " አለችው ። ዳግመኛ ስለ ስሟ ስጠይቀው እንደ ማታው እንዳይጮኽ በመፍራት...
የጨበጣትን እጁን ከእጇ አላቀቀና " እኔ
አዳም እባላለሁ። እሷ ደግሞ" አለ አልጋዉ ላይ ዟ ብላ ወደተኛችው ልጅ እየጠቆመ "ሄዋን ትባላለች" ብሎ ሌላ ወሬ ሊያወራ ሲል ተናዳ "አትቀልድ
ባክህ ትክክለኛ ስማችሁን ንገረኝ" አለችው ...
"ማለት?" አላት
"ማለትማ ስማችሁን በስርአት ንገረኝ"
" ነገርኩሽኮ" እየተባባሉ ሲጨቃጨቁ አንድ ጠና ያለ ዶክተር ሄዋን ክፍል
ገብቶ ካያት በኋላ ወደ አዳም ዞረና "አቶ አዳም ለወይዘሪት ሄዋን መድሃኒት
ያስፍልጋታል ። ነገ ማታ ትነቃለች የሚል ግምት አለኝ "ብሎት ሄደ ...
ነርስ ዲናም እንዳልቀለደ ገባት ። አዳም እና ሄዋን መገጣጠም ነው ወይስ
ለእራሳቸው አውጥተውት ነው..? ብላ ተገረመች ። አዳም በደስታ ጮቤ ረገጠ ። መቼም የሚያየው ያልመስለውን አይን ሊያይ ቀጠሮ ተስጥቶታል ። ሮጥ ሮጥ እያለ መራመድ ጀመረ... ዲና "የት ልትሄድ ነው
አለችው"
"መድሃኒቱን ልገዛ ነዋ " ፊቱ ላይ ደስታ ይነበባል ።
"አብርን እንሂድ " አለችው
ፈገግ ብላ ...
"ስራሽስ? "
"ፈረቃዬን ጨርሻለው። ከመውጣቴ በፊት ላያችሁ ነበር የመጣሁት ።
"እሺ እንሂድ" አላት አዳም እየተጣደፈ
እስታፍ ልብሷን ቀይራ መጥታ መንገድ ጀመሩ ።
መንገድ ላይ "አለሜ ልትነቃ ነው። አዎ ልትነቃ ነው ። እናትዬ ልትነቃ ነው " አለ ጮኽ ብሎ...
ዲና ግራ ገባት ። እንደመሳቅም እየቃጣት
" አረ ባክህ ዝም በል..ቆይ ይህቺ
ሴት ምን አይነት እድለኛ ብትሆን ነው እንዲህ ያለ አፍቃሪ የሰጣት። ...
አይ ሄዋን " አለች በውስጧ ስለሁለቱ ታሪክ ለመስማት እየጓጓች....

ይቀጥላል...

@ethio_leboled