Get Mystery Box with random crypto!

የዳምቢሳ ሞዮ ' DEAD AID ' የተሰኘው ዝነኛ መጽሐፍዋ ' ገዳይ ተራድኦ ' በሚል ርዕስ በአም | ልብወለድ Ethio_Fiction

የዳምቢሳ ሞዮ " DEAD AID " የተሰኘው ዝነኛ መጽሐፍዋ " ገዳይ ተራድኦ " በሚል ርዕስ በአምላክ ጎዳና ተተርጉሞ ለንባብ በቃ ::

አፍሪካ በሙስና ብቻ ወደ 150 ቢልዮን ዶላር በዓመት ታጣለች ::

20 % የሚሆነው የአፍሪካ ህዝብ በጠኔ ምክንያት የሞት አፋፍ ላይ ነው :: 

31 % የሚሆኑ ከሠሃራ በታች የሚገኙ ህፃናት የተመጣጠነ ምግብ አጥተው ቀንጭረዋል ::

ግማሽ ቢልዮን የሚሆነው የአፍሪካ ህዝብ አሁንም በመብራት እጦት ዳፈና ውስጥ ይኳትናል ::

50% የሚሆነው አፍሪካዊ በኮሌራ እና ተቅማጥ የመያዝ እድሉ ሰፊ ነው ።

አንዲት አፍሪካዊ ሴት ከአሜሪካዊት ሴት ጋር ስትነፃፀር 231 እጥፍ በወሊድ ወቅት የመሞት እድል አላት ::

25 ሚልዮኑ አፍሪካዊ የ "HIV" ታማሚ ነው። 600 ሚልዮኑ አፍሪካዊ ማንበብ እና መጻፍ የማይችል መሃይም ነው።

እኛ አፍሪካውያን ያልተረዳነው ዋናውና ዋናው ነገር  አፍሪካ ወደከፍታ የምትሻገረው በእርዳታና በሌሎች ችሮታ  ሳይሆን በጠንካራ የሥራ ባህል  በቴክኖሎጂ ፈጠራ እና በካፒታል ነው።

ቻይና 850 ሚልዮን ህዝቧን ከደህነት አረንቋ ያወጣችው በእርዳታ ሳይሆን በራሷ ስራ ነው!

በእርዳታ ያደገ ወይም የበለፀገ  አህጉር አይደለም ሃገር እንኳን የለችም :: የሚገርመው አሜሪካ ከቻይና ገንዘብ ትበደራለች ::  ከዛ የተበደረችውን ደግሞ ለአፍሪካ በእርዳታ መልክ ትሰጣለች! አሜሪካ ምን ያህል ብታስብልን ይሆን !?

ምንም ጥርጥር የለውም የአፍሪካ ሃብት የሚመዘበረው በእርዳታ መጋረጃ ነው።

በተጨማሪ ኢኮኖሚስት ዋሲሁን በላይ በመጽሐፉ ዙሪያ የሰራውን ትንተና  ተመልከቱት

ርዕስ - ገዳይ ተራድኦ
ደራሲ - ዳምቢሳ ሞዮ

Share -
@ethio_fiction

Comment -
@sam_lizu