Get Mystery Box with random crypto!

🌱መርጌታ መንግስቱ የባህል መዳኒት ቀማሚ 🌿

የቴሌግራም ቻናል አርማ esat_tv9 — 🌱መርጌታ መንግስቱ የባህል መዳኒት ቀማሚ 🌿
የቴሌግራም ቻናል አርማ esat_tv9 — 🌱መርጌታ መንግስቱ የባህል መዳኒት ቀማሚ 🌿
የሰርጥ አድራሻ: @esat_tv9
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.86K
የሰርጥ መግለጫ

ፈጣን መረጃዎችን ከኛ ዘንዳ ያገኛሉ

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-10-08 20:52:27 https://t.me/Esat_tv9
1.3K viewsDagi, 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 20:52:19
የ12ኛ ክፍል ፈተና ለመዉሰድ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የገቡ ስድስት ነፍሰጡር ተማሪዎች በሰላም ተገላገሉ

በትናንትናዉ እለት በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ልጇን በሰላም ከተገላገለችዉ ተማሪ ጽጌሬዳ አበራ በኋላ ትናንት አመሻሹን እና ዛሬ ተጨማሪ አምስት ነፍሰጡር እናቶች የ12ኛ ክፍል ፈተናቸዉን ለመዉሰድ በየገቡበት ዩኒቨርሲቲዎች እናት መሆናቸዉ ተገልጿል።

በደብረማርቆስ ፣ አምቦ ፣ ቡሌሆራ ፣ ቦረና እና ወራቤ ዩኒቨርስቲዎችም ተመሳሳይ ዜና ተሰምቷል። ከነዚህ ዉስጥም በቡሌሆራ ዩኒቨርስቲ የተገላገለችዉ ተማሪ መንታ ልጆችን በሰላም ወልዳለች።

በዚህም መሰረት አራት ወንድና ሶስት ሴት ልጆች በድምሩ ሰባት ህጻናት በዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ ተወልደዋል።
@ Esat_tv9
@Esat_tv9
1.3K viewsDagi, edited  17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 20:52:19
1.2K viewsDagi, 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 20:52:19
1.1K viewsDagi, 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 20:52:18
1.1K viewsDagi, 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 20:52:18
1.1K viewsDagi, 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 20:52:18
1.1K viewsDagi, 17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 06:39:03
#Gambella

" የአካባቢው ማህበረሰብ በተቻለው አቅም እራሱን እንዲጠብቅ አደራ እንላለን " - የጋምቤላ ክልል መንግስት

የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል፤ ኑዌር ዞን በከፈቱት ተኩስ 3 ሰዎችን ሲገድሉ ፤ አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ አፍነውን ወስደዋል።

የጋምቤላ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን እንዳሳወቀው በቀን 26/01/2015 ዓ/ም ከቀኑ 12 ሰዓት ገደማ ላይ በኑዌር ዞን ፤ በማኮይ ወረዳ በሎንጆክ ቀበሌ የሙርሌ ታጣቂዎች ተኩስ ከፍተው 3 ሰዎችን ሲገድሉ፤ አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ አፍነው ወስደዋል።

ይህ ድርጊት የተፈፀመበት ቦታ " ጎርፍ ካጠቃቸው " ቦታዎች አንዱ ሲሆን ህብረተሰቡን የማረጋጋት እና ታጣቂዎች ለመያዝ እየተሰራ መሆኑን ክልሉ አሳውቋል።

የክልሉ መንግስት ፤ የአካባቢው ማህበረሰብ በተቻለው አቅም እራሱን እንዲጠብቅ አደራ ብሏል።

የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጊዜ ድንበር ጥሰው እየገቡ በኑዌር ዞን እና አኝዋሃ ዞን በሰው ህይወት ላይ አደጋ ሲያደርሱ እና በርካታ ከብቶችንም ዘርፈው ሲወስዱ ቆይተዋል።

@Esatethiopiantv
@Esatethiopiantv
1.2K viewsDagi, edited  03:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 06:39:03
1.1K viewsDagi, 03:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 22:32:06
" ተማሪዎች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው ተርፈዋል ፤ ወላጆችም ተረጋጉ " - የሲግሞ ወረዳ

ዛሬ በጅማ ዞን ፤ ከሲግሞ ወረዳ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ጭኖ ወደ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ስጓዝ የነበረ አውቶብስ ተገልብጦ የትራፊክ አደጋ ደርሶ ነበር።

ነገር ግን ተማሪዎች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው መትረፋቸውን የወረዳው አስተዳደር አሳውቋል።

የተማሪ ወላጆችም ይህንን በማወቅ እንዲረጋጉ መልዕክት ተላልፏል።

መረጃው የሲግሞ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን / ሱልጣን ኢብራሂም / ነው።

በዚህ አጋጣሚ ወቅቱ ተማሪዎችን ወደ መፈተኛ ማዕከላት ከማድረስ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በመኖሩ አስሽከርካሪዎች በጥንቃቄ እና በእርጋታ እንዲያሽከረርክሩ በድጋሜ አደራ እንላለን።

@Esatethiopiantv
@Esatethiopiantv
1.1K viewsDagi, edited  19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ