Get Mystery Box with random crypto!

አብሰራ ገብርኤል ለማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ enatachn_mareyam — አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ enatachn_mareyam — አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @enatachn_mareyam
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.78K
የሰርጥ መግለጫ

እኔ #በእግዚአብሔር_ፊት የምቆመው #ገብርኤል_ነኝ
በቻናላናችን የሚሰጡ ነገሮች
መንፈሳዊ ትምህርቶች
መንፈሳዊ ምክሮች
መንፈሳዊ መዝሙር
መንፈሳዊ ጥያቄዎች
መንፈሳዊ ስዕልዎች
በየለቱ ስንክሳር
አስተያየት ካላቹ 👇👇👇
https://t.me/Enatemareyam21
https://t.me/Enatemareyam21

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-30 07:03:51
#ሊቀ_ሰማዕት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_አባቴ

፨ገድል፨
ገድል ያለመለመው ወንጌል የተባለው
#የጊዮርጊስ ስሙ እጅግ ያማረ ነው
አይደርቅ አይጠወልግ ሁሌም አበባ ነው
ሹመት ሽልማቱን ክብሩን ሁሉ ትቶ
ታስሮ ተገርፈ
#ለአምላኩ_ክብር ቀንቶ
ኧረ እንደምን ቻለው ያን ሁሉ መከራ
ተቆልቶ ተፈጭቶ እንደ እህል ሲዘራ
እኔስ ይደንቀኛል
#ገድልህን ሳስበው
ሰባት ዓመት በገድል ይኖራል እንዴ ሰው
ዛሬ ዛሬማ እጅግ ያሳዝናል
ለሰው ምላስ ብሎ ክሩን ይበጥሳል
ሰው ጌታውን ሲክድ ለስጋ እያዘነ
#ጊዮርጊስ_አባቴ_ለአምላኩ እስከሞት ታመነ
አክሊል የሚያስገኘው ይኸው ስለሆነ።

#እንደ_ኮከብ_ብሩህ
#እንደ_ሕፃን_ንጹህ

#_ሰናይ_ቅዳሜ

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
29 viewsብላቴና ዳዊት, 04:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 05:32:46
41 viewsባሕራን, 02:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 05:32:43


† እንኳን ለእናታችን ቅድስት መሪና ሰማዕት እና ቅዱስ ለንጊኖስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †


† ታላቋ ቅድስት መሪና ሰማዕት [SAINT MARINA THE GREAT] †


† እናታችን ቅድስት መሪና ስም አጠራራቸው ከከበረ : ተጋድሏቸው ካማረ ታላላቅ ሴት ሰማዕታት አንዷ ናት:: ተወልዳ ያደገችው ከዋናው ዘመነ ሰማዕታት በፊት በ፪ [2] ኛው መቶ ክ/ዘመን ሶርያ አካባቢ ነው:: አባቷ ዳኬዎስ የሚባል ጣዖት አምላኪ ቢሆንም እናቷ ግን ክርስቲያን ነበረች::

ነገር ግን እናቷ ገና በ፭ [5] ዓመቷ ሞተችባትና ለሞግዚት ተሰጠች:: የእግዚአብሔር ጥበብ ሆኖ ሞግዚቷ ደግ ክርስቲያን ነበረችና ለ፲ [10] ዓመታት ሃይማኖተ ክርስቶስን እና ምግባረ ጽድቅን አስተማረቻት:: ዕድሜዋ ፲፭ [15] ዓመት ሲሆን አባቷ ዳኬዎስ አረፈ::

በዘመኑ ዳኬዎስ የሚሉት [ቅዱስ መርቆሬዎስን የገደለው] ክፉ ንጉሥ ነበርና ክርስቲያኖችን አሳደዳቸው:: ይህን ዜና ቅድስት መሪና ስትሰማ ደስ አላት:: እጅግ ባማረ ንጽሕና እንደ ኖረች ሁሉ በክርስቶስ ስም ደሟን ለማፍሰስ አስባ ወደ ንጉሡ መኮንን ሔደች::

† አበው እንዳስተማሩን ከሴቶች ሰማዕታት በውበትና ደም ግባት እንደ ቅዱሳት :-

- መሪና
- አርሴማ እና
- ጣጡስ የሚያክል የለም:: ዐይንን ማፍዘዝ የሚችል ውበት ነበራቸው::

መኮንኑ መልኩዋን ዐይቶ ሰውነቱ ተናወጠ:: "ጣዖት አምልኪና የእኔ ሚስት ሁኚ" አላት:: እርሷ ግን መኮንኑን ከነ ጣዖቱ አቃለለችው:: "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ" አለችው::

መኮንኑ ካነጋገሯ የተነሳ ተቆጥቶ ይገርፏት ዘንድ አዘዘ:: መሬት ላይ ጥለው በብረት ዘንግ ቢመቷት አካሏ እየተቆረጠ ብዙ ደም ፈሰሰ:: ወስደውም ጨለማ ውስጥ ጣሏት:: ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወርዶ አድኗት: አጽንቷትም ዐረገ::

በማግስቱ በመጋዝ አካሏን ቆራርጠው ጣሉ:: ዳግመኛ ሊቀ መላእክት አዳናት:: ወደ ጨለማ ክፍል ወስደው ሲጥሏት ትልቅ ዘንዶ መጣባት:: እጆቿ ተዘርግተው እጸለየች ዋጣት:: እርሷ ግን ጸሎቷን ቀጠለች:: ከደቂቃዎች በሁዋላ ግን ዘንዶው ለ፪ [2] ተሰነጠቀና እጆቿ እንደተዘረጉ ወጣች::

በሌላ ቀን ግን ሰይጣን ፊት ለፊት መጥቶ ታገላት:: ከሰማይ ነጭ ርግብና መስቀል ወርዶላታልና አልቻላትም:: ከእግሯ በታች ጥላ ደጋግማ ረገጠችው:: ሰይጣንም በሐፍረት እየጮኸ ሔደ::
"ለሰይጣን ኬደቶ ከመ አሣዕን በእግር" እንዲል:: [እንዲህ ነበሩ የቀደመው ዘመን እናቶቻችን]

መኮንኑ ከክርስትና ያስወጣት ዘንድ በትልቅ ጋን ውሃ አስፈልቶ "በዚያ ላይ ቀቅሏት" አለ:: ድንገት ግን ከሰማይ ነጭ ርግብ ወርዳ: ውሃውን አቀዝቅዛ : ፫ [3] ጊዜ በውሃው አጠመቀቻት:: [እስከዚህ ሰዓት ድረስ አልጠመቀችም ነበርና]

ርግቧ የብርሃን ልብስ አልብሳ: አክሊለ ክብር ደፋችላት:: መኮንኑ ተስፋ ስለ ቆረጠ "አንገቷን በሰይፍ ምቱ" አለ:: በዚያች ሰዓት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርዶ "ብጽዕት መሪና ብጽዐን ይገባሻል" አላት::

"ስምሽ በሚጠራበት: መታሰቢያሽ በሚደረግበት ሁሉ በዚያ ረድኤት: በረከት ይበዛል:: አንቺን ያከበረውን አከብረዋለሁ:: ከርስትሺም አስገባዋለሁ" ብሏት ጌታችን ዐረገ::

ወታደሮቹ አንገቷን በሰየፉ ጊዜ ታላቅ መነዋወጽ ሆነ:: ድውያን ተፈወሱ: ዕውሮች አዩ: አንካሶች ረቱ: የማይሰሙትም ሰሙ:: ቅዱሳን መላእክትም ከሰማያት ወርደው የቅድስት መሪናን ነፍስ በዝማሬ አሳረጉ::


† ቅዱስ ለንጊኖስ ሰማዕት †

† ለንጊኖስ ማለት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስብከት ዘመን የዺላጦስ ወታደር የነበረ ሰው ነው:: ስለ ጌታችን ተአምራት በየጊዜው ይሰማ ነበር:: ሔዶ እንዳያገኘው ግን አይሁድን ይፈራ ነበር:: እነርሱ "በክርስቶስ ያመነ ሁሉ ከምኩራብ ይባረር" ብለው ነበርና:: [ዮሐ.፱፥፳፪] (9:22)

ጌታችን በተሰቀለባት ዕለተ ዐርብ ግን ጭንቅ ሆነበት:: ጌታን እንዲሰቅሉ ከታዘዙ ወታደሮች እንደ አንዱ ተመርጦ ነበርና በዘዴ "አሞኛል" ብሎ እስከ ፱ [9] ሰዓት ድረስ ቆየ::

በሁዋላ ግን አይሁድ "በክርስቶስ ሞት ያልተባበረ ሁሉ ወንጀለኛ ነው" የሚል አዋጅ በማስነገራቸው እየፈራ ቀራንዮ ሲደርስ "ጐኑን ውጋው" ብለው ረዥምና ጥቁር ጦር ሰጡት:: ለንጊኖስ ወደ ጌታችን ዐይን ተመለከተ:: እያየው እንዳልሆነ ገመተ::

ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው በባሕርይ ሥልጣኑ ለይቷልና ጦሩን ጨብጦ ወደ ጌታ ጐን ልኮ ወጋው:: ከጌታ ቀኝ ጐንም በ"ለ" አምሳል ትኩስ ደምና ውሃ ፈሰሰ:: አንዷ ፍንጣቂ ሔዳ የታወረች ዐይኑ ላይ ዐርፋ ዐይኑን አበራች::

ለለንጊኖስ ታላቅ ደስታ ሆነ:: ለእኛ ግን ማየ ገቦና ደመ ገቦ ፈለቀልን:: የጌታችን ትእግስቱና ቸርነቱ ግን ይደንቃል::
"ከመ ኢየሐስብ ቦቱ ዘኩናተ እዱ ርግዘቶ::
በኃጣውኢሁ ለዘኢፈቀደ ሞቶ::
ምሕረቶ እሴብሕ ወዐዲ ትዕግስቶ::" እንዳሉ ሊቃውንት::

ጌታችን ከተነሳ በሁዋላ ለንጊኖስ ወደ ቅዱስ ዼጥሮስ ዘንድ ሒዶ ስለ እውነት : ስለ ሃይማኖትም ተማረ:: ተጠምቆ: ምድራዊ ወታደርነቱን ትቶ እየሰበከ ከኢየሩሳሌም ወደ ቀዸዶቅያ ወረደ:: ለዘመናትም ጌታችን ክርስቶስን በሥርዓተ ወንጌል አገለገለ::

በመጨረሻም በጢባርዮስ ቄሣር ዘመን አይሁድ አሳደዱት: አንገላቱት:: የነርሱ ወገን ስለነበረም መከራ አጸኑበት:: የጽድቅ አርበኛና የክርስቶስ ሐዋርያ ቅዱስ ለንጊኖስ ግን ጸና:: በዚህች ዕለትም አይሁድ አንገቱን ቆርጠውት ለሰማዕትነት በቃ:: ቅዱሱ በሕይወቱም በዕረፍቱም ተአምራትን ሠርቷል::

† እግዚአብሔር በቸር ጥሪው ሁላችንም ወደ ቀናው የጽድቅ ጐዳና ይጥራን:: ከሰማዕታቱም ረድኤት በረከት ይክፈለን::



† ሐምሌ ፳፫ [23] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

፩. ቅድስት መሪና እናታችን [ታላቋ ሰማዕት]
፪. ቅዱስ ለንጊኖስ ሐራ [ሐዋርያና ሰማዕት]
፫. ቅዱስ አብጥልማዎስ

† ወርኀዊ በዓላት

፩. ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
፪. ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
፫. ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን [ንጉሠ እሥራኤል]
፬. አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
፭. ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ
፮. አባ ሳሙኤል
፯. አባ ስምዖን
፰. አባ ገብርኤል

† "ወደ ጌታ ኢየሱስ በመጡ ጊዜ ግን እርሱ ፈጽሞ እንደ ሞተ አይተው ጭኑን አልሰበሩም:: ነገር ግን ከጭፍሮች አንዱ ጐኑን በጦር ወጋው:: ወዲያውም ደምና ውሃ ወጣ:: ያየውም መስክሯል : ምስክሩም እውነት ነው:: እናንተም ደግሞ ታምኑ ዘንድ : እርሱ እውነት እንዲናገር ያውቃል:: ይህ የሆነ:-
"ከእርሱ አጥንት አይሰበርም" የሚል የመጽሐፍ ቃል እንዲፈጸም ነው:: ደግሞም ሌላው መጽሐፍ:-
"የወጉትን ያዩታል" ይላል::" † [ዮሐ.፲፱፥፴፫] (19:33)


† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †


" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን":: /የቅዱሳንን ዜና [ታሪክ] እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/


[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


41 viewsባሕራን, 02:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 19:12:24
150 viewsባሕራን, 16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 19:12:16 ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


ቦሩ ሜዳ !


አስደናቂው የሊቃውንት ምላሽ !

-------------------------------------------------

የመጀመሪያው ''ቦሩ ሜዳ'' ጉባዔ በሐሰተኛ መምህራን ፣ አጥማቂያንና ባህታዊያን ላይ ከምዕመናን ለተነሱ ጥያቄዎች በሊቃውንትና በመምህራን መልስ በመሥጠት ተካሂዷል::

- ሐሰተኛ አጥማቂዎች እነማን ናቸው ?
- ሐሰተኛ አጥማቂዎችን በምን ለይተን እንወቃቸው ?
- ለምን በቤተክርስቲያን ገብተው ያጠምቃሉ ?
- የእግዚአብሔርን ፣ የእመቤታችንንና የቅዱሳንን ስም እንዴት ይጠራሉ ?
- "ጹሙ ጸልዩ ስገዱ" የሚሉን አባቶች እንዴት ሐሰተኛ ይባላሉ ?
- ሐሰተኛ አጥማቂዎች ለምን አይወገዙም ?

ምላሹን እነሆ ከታች ቀርቧል። ይከታተሉ !


" ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" [ይሁ.፩፥፫]

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

ዳታ ተጠቃሚዎች ኢትዮ ቴሌኮም የሰጠውን ስጦታ ይጠቀሙ !


145 viewsባሕራን, 16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 12:47:21 መንፈሳዊ ትረካ እና አጫጭር ጽሑፎች:
የማንንን ስብከት ፈልገው አጥተዋል ሁሉንም በአንድ ቻናል ይዘንላችሁ መጥተናል ከ58ሺህ በላይ ተከታይ ያለው ቻናል ከፍተናል

➥የመምህር ምህረተአብ አሰፋ ስብከት

➥የዲያቆን ሔኖክ ኃይሌን ስብከት

➥የመጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ገብረ ኪዳንን ስብከት

➥የቀሲስ ዶክተር ዘበነ ለማን ስብከት

➥የመጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ ትምህርቶች

➥የዲያቆን ዳንኤል ክብረትን እይታ

➥የሊቀ ሊቃውን ዕዝራ ሐዲስ ስብከት

ቻናሉን ለመቀላቀል ሰማያዊውን ይጫኑ

https://t.me/+WQa32Ma1f4w5NDNk

https://t.me/+WQa32Ma1f4w5NDNk

https://t.me/+WQa32Ma1f4w5NDNk

199 viewsማኅቶት ፕሮሞሽን 1000_5000, 09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 11:04:04
166 viewsባሕራን, 08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 11:04:01


[ ሥራህን ሥራ ! ]




" ጌታ ለእያንዳንዱ ሰው ሥራ ሰጥቶታል ያንን መስራት የእሱ ፈንታ ነዉ። ቢቻለዉ እሱን ማገድ የዲያብሎስ ሥራ ነዉ። በእርግጥ ሥራዉን እግዚአብሔር እንደሰጠህ ያህል ሰይጣን ሊያግድህ ይሞክራል። ሌላ ነገር በበለጠ ደስ የሚያሰኝ ሊያቀርብልህ ይጥራል። በዓለማዊ ተስፋዎች ያባብልሃል የሐሜት ጎርፍ ያስወርድብሃል። ደራሲያን እንዲጠይቁህ እጅግ ስመ ጥሩ ሰዎችም በክፋ እንዲናገሩብህ ይጠቀምባቸዋል።

ጲላጦስ ፥ ሄሮድስ ፥ ሀናንያ ፥ ቀያፋ ሁሉም በአንተ ላይ ያድማሉ . . . አንተ ግን በፀና ውሳኔ በማያወላውል ቅናት በመጨረሻ ላደርገው የሰጠኽኝን ስራ ፈፀምኩ ሃይማኖቴንም ጠበቅሁ ለማለት እስክትችል ድረስ የሕይወትህን ዓላማ እና የተፈጠርክበትንም ግብ ተከተል።"

[ ሥራህን ሥራ ! ]


[ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ]

[ 1933 ዓ.ም - ሐምሌ 22/ 1982 ዓ.ም ]

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


171 viewsባሕራን, 08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 10:25:40
161 viewsባሕራን, 07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ