Get Mystery Box with random crypto!

አብሰራ ገብርኤል ለማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ enatachn_mareyam — አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ enatachn_mareyam — አብሰራ ገብርኤል ለማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @enatachn_mareyam
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.78K
የሰርጥ መግለጫ

እኔ #በእግዚአብሔር_ፊት የምቆመው #ገብርኤል_ነኝ
በቻናላናችን የሚሰጡ ነገሮች
መንፈሳዊ ትምህርቶች
መንፈሳዊ ምክሮች
መንፈሳዊ መዝሙር
መንፈሳዊ ጥያቄዎች
መንፈሳዊ ስዕልዎች
በየለቱ ስንክሳር
አስተያየት ካላቹ 👇👇👇
https://t.me/Enatemareyam21
https://t.me/Enatemareyam21

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-29 07:28:00
#ኦ_ፍጡነ_ረድኤት እምሩፀተ ነፋስ ወዓውሎ፤ ለዘይጼውዓከ በተወክሎ፤
#ጊዮርጊስ ቅረብ ለምሕረት ወለተሣህሎ፤ ተወከፍ ወትረ ጸሎትየ ወቃለ ጽራሕየ ኵሎ፤ እስመ ልበ አምላክ ርኅሩኅ በኀቤከ ሀሎ፤»

#ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሆይ አንተን በመተማመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከአውሎ ነፋስ ይልቅ በተፋጠነ ሩጫ ነው እኮን፤ #ጊዮርጊስ ሆይ የዘወትር ጸሎቴን የቃሌን የልመና ጩኽት ትቀበል ዘንድ ለይቅርታና ለምሕረትህ ፈጥነህ ወደ እኔ ቅረብ፤”


#መልካም__ቀን

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
604 viewsብላቴና ዳዊት, 04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 07:44:04
#ፀሐይ_ብርሃን ካልሰጠች ፀሐይ አትባልም፤ ብርሃን አለመስጠት ተፈጥሮዋ አይደለምና፡፡ እንስሳት ካልተነፈሱ እንስሳት አይባሉም፤ መተንፈስ ተፈጥሮአቸው ነውና፡፡ ዓሣ ከውኃ ከወጣ ሕይወት ያለው ዓሣ መኾኑ ይቀርና ይሞታል፡፡ አንድ ክርስቲያንም እውነተኛ ክርስቲያን የሚባለው፡-

1.
#ሲጸልይ_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በወልድ ውሉድ በክርስቶስ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስም መንፈሳዊ መባል ነውና፡፡ ልጅ ከኾኑ ደግሞ አባትን ማናገር ክርስቲያናዊ ተፈጥሮ ነውና፡፡

2.
#ሲያመሰግን_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት እግዚአብሔር ፈጣሬ ዓለማት ነው ብሎ ማመን ነውና፡፡ ስለዚህ ለአንድ ክርስቲያን የሰማይና የምድር ውበት እየተመለከተ እግዚአብሔርን ማመስገኑ ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነው፡፡

3.
#ሲመጸውት_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት ሀብት ኹሉ ከእግዚአብሔር እንደ ኾነ መመስከር ነውና፡፡ ስለዚህ ራስን እንደ መልእክተኛ አድርጎ በመቁጠር ያለውን ለሌላው ማካፈል ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡

4.
#ቅዱሳት_መጻሕፍትን_ሲያነብ_ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በመንፈስ ቅዱስ ሀብት ደስ የሚሰኝ ነውና፡፡ ይህን ለማድረግ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ በቅዱሳት መጻሕፍት በኩል ሲናገር መስማት ለአንድ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡

#አራቱ_የንስሐ_መንገዶች

#መልካም_ዕለተ_ሰንበት

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
639 viewsብላቴና ዳዊት, 04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 21:21:22 #ብዙ_አገልጋዮች የተሰጠንን ብዙ ነገር ትተን ትንሿን ነገር ለመጠበቅ ስንሮጥ ብዙ ጸጋዎቻችንን እናጣለን....ለመዘመር ብቻ ስንሯሯጥ ጸሎትን ስግደትን ትህትናን ወርውረን እንሰብራቸዋለን...ለመማር ብቻም ስንሮጥ ፍቅርን ቸርነትን ይቅርታን ወርውረን እንሰብራቸዋለን...አገልግሎት ብቻ ላይ ስንሮጥ #ከጸሎት ሕይወት ፈጽመን እንወጣለን፡፡ #ምን_ለማለት ፈልጌ ነው"... #ያለ_ጸሎት ከሚሆን አገልግሎት ያለ አገልግሎት የሚደረግ #ጸሎት የበለጠ ነው ..." ብለዋል #አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ ለማለት ነው፡፡
497 viewsብላቴና ዳዊት, 18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 07:47:12
" #አዎ_እመቤቴ_ነሽ "

ምን ነው ዛሬ ሊቁ ቅዱስ ያሬድን በሆንኩ፣
ኤፍሬምንም በተካሁ ሕርያቆስን በመሰልኩ፣
ገብርኤልን በሆንኩኝ ሰላም ለኪን በዘመርኩ።
ንዒ ንዒ ባልኩሽ ቁሜ አባ ጊዮርጊስን ተክቼ፣
ሰቆቃሽንም በጻፍኩ ጽጌ ድንግልን ሰምቼ።
አንድም በራዕይ ሆኖ ወይንም ሌሊት በህልሜ፣
ከፊትሽ ላይ ሰግጄ እመቤቴ ባልኩሽ ቁሜ።

#አዎ_አመቤቴ_ነሽ..!!!

አባ ጊዮርጊስን አልሁን የያሬድም ይቅርብኝ፣
አባ ጽጌ ድንግልን አልሆን ኤፍሬምንም አታሳይኝ፣
ሕርያቆስን ሁኜ ባልቀኝም ቅዳሴ፣
#እመቤቴ ልበልሽ በምችለው በራሴ።

#አዎ_እመቤቴ_ነሽ..!!!

ንግስት አለሽ ዳዊት ቀድሞ፣
ሙሽራ አለሽ ልጁ ቆሞ፣
የተነበየልሽ ነቢዩ በትንቢት እንቅልፍ አልሞ፣
የታደሰብሽ ስምዖን የበኩር ልጂሽን ስሞ።
ድንግልም እናትም ሆነሽ የረቀቀብሽ ምስጢሩ፣
ሰማይ መሬትን ሆነሽ የልዑል አምላክ ሀገሩ፣
አሁን ምንድን ነው ነውሩ ስለ ቅድስናሽ መንገሩ።
ስለ ማርያም ማውራቱ ስለ ጽዮን ማስተማሩ?

#አዎ_እመቤቴ_ነሽ...!!!

ድምጽሽን የሠማሁት ከእናቴ ማህጸን ስወጣ፣
ሀኪም ቤት ሳይኖር ቀድሞ አምቡላስም ሳይመጣ፣
እኔ ለመውለድ በምጥ ስትጨናነቅ እናቴ፣
ጎረቤቶቹ ቁመው እያሉ ነበር "
#እመቤቴ
የሰማሁትን ቀድሜ እኔም እላለሁ እንደናቴ
ይህን ታላቅ ስም እንቁዕ የሚባለውን "
#እመቤቴ !"

#አዎ_እመቤቴ__ነሽ.!

አቅሙ ኑሮኝ ባልደርስም አዲስ ቅኔና ዜማ፣
ባልሰማቼውም ምስጋናሽን መላእክቱንም ከራማ፣
የደረሱትን አባቶቼ የሚገባውን ከአንጄቴ፣
" ሰአሊ ለነ "ልበልሽ ፍቀጂልኝ እመቤቴ

#ሰናይ___ቅዳሜ

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
743 viewsብላቴና ዳዊት, 04:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:46:35 በዚህ ምድር ስኖር #ከእውነት በቀር የፈለግሁት ነገር የለም ። መንገዱን አግኝቼዋለሁ ብዬ አሰብኩ ። #እውነት ለማግኘት የማያቋርጥ ትግልና መፍጨርጨር አደረኩ ። የተረዳሁት ግን #እውነት ማግኝት ማለት እራስን ማወቅና መዳረሻንም መረዳት ማለት ነው
527 viewsብላቴና ዳዊት, 18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 08:48:25
#___ወዳጄ_!!

#ጥዋት_ስትነሳ ጊዜ ያለህ ሰማይን መጨበጥ ፣የምትችል ነው የሚመስልህ፣ነገር ግን ማታ ስትቀመጥ ምንም እንዳላደረክ ስታስብ ቀኖችህ #በከንቱ እንደባከኑ ሲገባህ እጂግ በጣም ታዝናለህ።

#ወዳጄ ይሄውልህ ጥዋት፣ለአንተ #የወጣትነትህ ጊዜ ነው።ማታ ደግሞ #የእርጂናህ ጊዜ ነው። ታዲያ ወዳጄ ጥዋት፣ወጣትነተህ ብዙ ጊዜ ያለህ ነገሮችን ቀስ ብለህ ማድረግ ያለብህ እየመሰለክ #ጊዜህን ሳታውቀው ማታ ላይ ይደርሳል እርጂና ይመጣል።ያኔ ምነው ነገሮችን ጥዋት ባደርጋቸው እንዳትል በሕይወት ዘመንህ አምላክህ ለአንተ መመሪያ ይሆን ዘንድ፣ቀንና ማታ አድረጎ ፈጥሮልሃል።

ቀን፣ጥዋት ስትነሳ ማታ እንደሚመጣ አስብ ወጣት ሳለህ እርጂና እንደሚመጣ አስተውል።ያኔ በሕይወት ዘመንህ ምን ማድረግ እንዳለብህ ወዴት እንደምትሄድ ስለምታውቅ ወጣትነትህ ጥዋትህ ትጠቀማለህ።


#__ሰናይ__ቀን

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
1.1K viewsብላቴና ዳዊት, 05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 21:24:21 #ወዳጄ !!!

ልብህን የሚሰብረው ከሰዎች ብዙ መጠበቅ ነው፤ ስለዚህ ከሰዎች ብዙ አጠብቅ። እህቴ የሚከፋሽ ሌሎች የሚያደርጉልሽን ጠብቀሽ ስላላገኘሽ ነው። ከሰው መጠበቁን አቁመን ደስታችንን ከፈጣሪና ከራሳችን ልብ ውስጥ ማግኘት ነው ያለብን፤ ያኔ አንዱን ቀን ደስ ብሎን ሌላኛውን ቀን አይከፋንም ምክንያቱም ደስታችን ሌሎች ላይ ጥገኛ አይደለም።
581 viewsብላቴና ዳዊት, edited  18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 09:59:06 #የአራቱ_ወንጌላት አንድምታ ትርጓሜ

ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስ፣ ዮሃንስ

ጊዜን በንባብ አሳልፉ አይናቹ ከቅዱሳን መፃህፍት አይለዩ
518 viewsDam ፯, edited  06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 09:57:22
1. ማቶዎስ = #በሰው ገጽ ተመስሏል፣ የክርስቶስን በስጋ ከአብርሃም ከዳዊት መምጣት ልደቱን በመዘርዘር አስረድቷልና፥፥

2. ማርቆስ = #በአንበሳ ተመስሏል፣ ግብጽ የነበሩትን የአንበሳ ጣኦታት በስብከቱ አፍርሶ አንበሳ የተባለ ክርስቶስን ሰብኳልና፥፥

3. ሉቃስ = #በላም ገጽ ይመሰላል፣ ጌታ ኢየሱስ በከብቶች ማደርያ መወለዱን ከሌሎች ይልቅ አስፍቶ ስለጻፈ፥፥

4. ዮሃንስ = #በንስር ይመሰላል፣ ንስር ከሌሎች አእዋፍ ሁሉ ተለይቶ ወደ ላይ መጥቆ ይበራል። በላይም ሆኖ በመሬት ያሉትን ረቂቃን ነገሮች አጣርቶ መመልከት ያውቅበታል። ወንጌላዊው ዮሃንስም ከሌሎች ወንጌላውያን አጻጻፍ በተለየ በምስጢረ ስላሴ ይጀምርና ስለ ተዋህዶም ሲጽፍ ወደ ላይ መጥቆ በማሰብ ቅድመ ዓለም ስለነበረው ቃል ይተርክና ዝቅ ብሎ "ያም ቃል ስጋ ሆነ" በማለት ይጽፋል።
459 viewsDam ፯, edited  06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 07:31:42
#እኔ_በእግዚአብሔር_ፊት_የምቆመው_ገብርኤል_ነኝ (ሉቃ 1፥19)
#ይህ_ገብርኤል_ነው
በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ብርሃን የገለጸና የሰበከ
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
የነቢያትን ትንቢት የፈጸመ፤ የክርስቶስን ልደት ለድንግል ያበሰረ
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
ዳንኤልን ከአነብስት ያዳነው
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
ሠለስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ያዳናቸው
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
ወደ ዘካሪያስ የተላከ የዮሐንስ ልደት ያበሰረ
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
ወደ ዮሴፍና ወደ ኒቆዲሞስ የተላከ
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
ቂርቆስና ኤናቱ ኢየሉጣን ከእቶን እሳት ያዳናቸው
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
ሰብአ ሰገልነረ በኮከብ ምልክት የመራቸው
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
ድንግል ማርያሜና ሕፃኑን ክርስቶስን በምድረ በዳ በስደታቸው የመራ
#ይህ_ገብርኤል_ነው ።
የብርሃን ወርቅ የተቀዳጀ
#ገብርኤል_ነወ ።
የአሸናፊና የኀኃይል መልአክ
#ገብርኤል_ነው ።
ነበልባላዊ ዖፈ ሰማይ
#ገብርኤል_ነው ።
#የመልአኩ_የቅዱስ_ገብርኤል_ጥበቃና_ረድኤት_አይለየን አሜን

#ገብርኤል_ገብርኤል ሲሉ ማማሩ ማማሩ ከእሳት ያወጣል በያዘው #መስቀሉ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል #ሀገራችንን_ይጠብቅልን አሜን አሜን

#_ሰናይ_ቀን

አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ ለማግኘት //

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
1.2K viewsብላቴና ዳዊት, 04:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ