Get Mystery Box with random crypto!

እመ-ብዙኃን ሰ/ት/ቤት

የቴሌግራም ቻናል አርማ emebizuhan_sunday_school — እመ-ብዙኃን ሰ/ት/ቤት
የቴሌግራም ቻናል አርማ emebizuhan_sunday_school — እመ-ብዙኃን ሰ/ት/ቤት
የሰርጥ አድራሻ: @emebizuhan_sunday_school
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 377
የሰርጥ መግለጫ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ /ን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በቃሊቲ ስርጢ ቅ/ቅ/ድንግል ማርያም ቤ/ን እመ-ብዙኃን ሰ/ት/ቤት የተከፈተ ልዩ ልዩ የቤተክርስቲያናችንና የሰንበት ትምህርት ቤታችን ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት የቴሌግራም ገጽ ነው።
ኑ ለታሻለ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት በጋራ እንስራ!!

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-08 18:03:53
ወርሐዊ የአንድነት ጉባኤ

✥ እሑድ ✥

ሐምሌ 3

✥ጸሎት

✥ልዩ መርሃግብር (ስልጠና)

ጠዋት ከ3:00 ጀምሮ

✥ በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ
271 views15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 19:12:08
".....ዮሐንስ ሆይ! ራጉኤል በትጋቱ፣ ኢዮብም በጽድቁ ቢመኙም ኾነ ቢጨነቁ እንደ አንተ የሚነድ እሳትን (መለኮትን) ሊያጠምቁ አልተቻላቸውም››

(መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ)
268 views16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 19:09:02 ልደተ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ

ሰኔ 30

እንኳን አደረሳችሁ

ዮሐንስ ማለት ‹‹እግዚአብሔር ጸጋ ነው›› ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ፍሥሐ ወሐሴት (ተድላና ደስታ) ይለዋል፤ ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና (ሉቃ. ፩፥፲፬)፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ሰኔ ፴ ቀን የተወለደበት፤ መስከረም ፩ ቀን ቃል ኪዳን የተቀበለበት፤ መስከረም ፪ ቀን በሰማዕትነት ያረፈበት፤ ጥር ፲፩ ቀን ጌታችንን ያጠመቀበት፤ የካቲት ፴ ቀን ራሱ የተገኘችበት፤ ሚያዝያ ፲፭ ቀን ራሱ ያረፈችበት (ነፍሱ የወጣችበት)፤ ሰኔ ፪ ቀን ደግሞ ፍልሰተ ዐፅሙ (ዐፅሙ የፈለሰበት) በዓል በቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ ይከበራል፡፡



በቅዱስ ሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ አንድ፣ ከቍጥር አንድ ጀምሮ እንደ ተገለጸው ካህኑ ዘካርያስ እና ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ዅሉ በመፈጸም ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ፡፡ ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፡፡ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድም እግዚአብሔርን ዘወትር ይማጸኑት ነበር፡፡

ካህኑ ዘካርያስ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ዕጣን በማሳረግ ላይ ሳለም የእግዚአብሔር መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ጸሎቱ እንደ ተሰማና ሚስቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ እንደምትወልድ፤ ስሙንም ዮሐንስ እንደሚለው፤ በመወለዱም ብዙዎች እንደሚደሰቱ፤ ልጁም በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ እንደሚኾን፤ የወይን ጠጅ እና የሚያሰክር መጠጥ እንደማይጠጣ፤ እንደዚሁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሞላበት ነገረው፡፡

✥ ✥ ✥ ✥ ✥

ካህኑ ዘካርያስም መልአኩን ‹‹እኔ ሽማግሌ ነኝ፤ ሚስቴም አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ?›› አለው፡፡ መልአኩም ‹‹እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፤ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፡፡ እነሆም በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ ይህ ነገር እስከሚኾን ቀን ድረስ ዲዳ ትኾናለህ፤ መናገርም አትችልም›› አለው፡፡

ከውጪ ቆመው ጸሎት ሲያደርጉ የነበሩት ሕዝብም ዘካርያስን ከቤተ መቅደስ እስኪወጣ ይጠብቁት ነበር፤ በመዘግየቱም ይደነቁ ነበር፡፡ ከቤተ መቅደስ በወጣም ጊዜ ሊያናግራቸው ባለመቻሉ ይጠቅሳቸው ነበር፡፡ በኹኔታውም በቤተ መቅደስ ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፡፡ እርሱም ድዳ ኾኖ ኖረ፡፡ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸምም ወደ ቤቱ ሔደ፤ ከሁለት ቀን በኋላም አረጋዊቷ ቅድስት ኤልሳቤጥ ፀነሰች፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም በመካንነቷ ከሰዎች የሚደርስባት ሽሙጥ ተወግዷላታልና ‹‹እግዚአብሔር በዚህ ወራት ከሰው ስድቤን ያርቅ ዘንድ እንዲህ አደረገልኝ›› ስትል ለአምስት ወራት ተሸሸገች፡፡

✥ ✥ ✥ ✥ ✥

የመውለጃዋ ቀን ሲደርስም ዘመነ ብሉይ ሊፈጸም፣ እግዚአብሔር ሰው ሊኾን (በሥጋ ሊገለጥ) ስድስት ወራት ሲቀረው፣ ሰኔ ፴ ቀን ንዑድ፣ ክቡር የኾነው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ፡፡ ዘመዶቹ ስሙን በአባቱ መጠርያ ‹ዘካርያስ› ሊሉት ቢወዱም እናቱ ግን ‹‹ዮሐንስ ይባል›› አለች፡፡ የመልአኩን የብሥራት ቃል ባለመቀበሉ አንደበቱ ተይዞ የነበረው ካህኑ ዘካርያም ስሙ ‹ዮሐንስ› ይባል ብሎ ሲጽፍ አፉ ተከፈተ፤ አንደበቱም ተፈታ፡፡

በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶም ‹‹… አንተ ሕፃን ሆይ! የልዑል ነቢይ ትባላለህ፤ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሔዳለህና፡፡ የኀጢአታቸው ስርየት የኾነውን የመዳን ዕውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፡፡ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፡፡ ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል፤ እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል፤›› በማለት የቅዱስ ዮሐንስን ነቢይነት እና አጥማቂነት፣ እንደዚሁም የክርስቶስን የማዳን ትምህርት አብሣሪነት የሚመለከት ትንቢት አስቀድሞ ተናገሯል (ሉቃ. ፩፥፶፯-፸፱)፡፡

✥ ✥ ✥

በአጠቃላይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ከአዲስ ኪዳን አበው አንዱ የኾነ፣ ንጹሓን ነቢያት፣ ቅዱስ ገብርኤልና አባቱ ዘካርያስ ትንቢት የተናገሩለት፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ ቅኑት እንደ ገበሬ፣ ጽሙድ እንደ በሬ ኾኖ እግዚአብሔርን ያገለገለ፤ በፍጹም ልቡ ዓለምን የናቀ፤ ከተድላዋና ከደስታዋም የተለየ፤ አምላክን ለማጥመቅ የታደለ

ሐዋርያ፣ መምህር፣ ሰማዕት፣ ባሕታዊ፣ ነቢይ፣ ጻድቅ ነው፡፡

ሊቁም ከመላእክት፣ ከነቢያት፣ ከካህናት፣ ከሐዋርያት መካከል እንደርሱ መለኮትን ለማጥመቅ የተመረጠ አለመኖሩን በመጥቀስ

‹‹… ዮሐንስ ከማከ ሶበ ፈተዉ ወጽሕቁ፤ እሳተ ነዳዴ ኢተክህሎሙ ያጥምቁ፤ ራጉኤል በትጋሁ ወኢዮብ በጽድቁ፤ …

ዮሐንስ ሆይ! ራጉኤል በትጋቱ፣ ኢዮብም በጽድቁ ቢመኙም ኾነ ቢጨነቁ እንደ አንተ የሚነድ እሳትን (መለኮትን) ሊያጠምቁ አልተቻላቸውም››

ሲል ታላቅነቱን መስክሮለታል (መልክአ ዮሐንስ መጥምቅ፣ ለአዕይንቲከ)፡፡

የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱ ይደርብን፤ ጸሎቱ ይጠብቀን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ምንጭ፦
ማኅበረ ቅዱሳን ድረገጽ
መጽሐፈ ስንክሳር፣ ሰኔ ፴ ቀን፤
የሉቃስ ወንጌል አንድምታ ትርጓሜ፣ ሉቃ. ፩፥፩-፹፤
ገድለ ዮሐንስ መጥምቅ፡፡

@Emebizuhan_sunday_school
✥ ✥ ✥ ✥ ✥

እመ-ብዙኃን ሰ/ት/ቤት

"እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም ይናገራል፤
ሰው ግን አያስተውለውም።" ኢዮ 33÷14
   
238 viewsedited  16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 19:08:35
207 views16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 18:07:49
✥ እንኳን አደረሳችሁ✥

" ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ ማንም የለም"
ሉቃ ፯:፳፰)

ሰኔ ፴ (30)
ሀሙስ

ልደተ መጥምቀ መለኮት
ቅዱስ ዮሐንስ

በዓለ ንግሥ

በደብራችን በቃሊቲ ስርጢ ቅ/ቅ ድንግል ማርያም ቤ/ክርስቲያን

#share #share
548 viewsedited  15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 13:04:33
የጸሎት መርሃግብር

✥ ዘወትር ረቡዕ ✥

ከምሽት ከ12:00 ጀምሮ

በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ

የዛሬ የጸሎት መርሃግብር እደተጠበቀ ነው ሁላችሁም እንደትገኙ!!!

እመ - ብዙኃን ሰ/ት/ ቤት
443 viewsedited  10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:06:49
355 views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:06:49
በዛሬ ዕለት የእናታችን የእመቤታችን በዓል እና ህንፀታ ቤተክርስቲያን ባማረ በደመቀ እንዲሁም እጅግ በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ተከብሮ ውሏል!!

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን!!!
ከእመቤታችን ረድኤት በረከት አይለየ አሜን!!

እመ-ብዙኃን ሰ/ት/ ቤት
310 views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:06:49
330 views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 06:53:01
"ወንሰግድ ውስተ መካን ኀበ ቆመ እግረ እግዚእነ.......

"ወደ ማደሪያዎቹ እንገባለን፤ እግሮቹ በሚቆሙበት ስፍራ እንሰግዳለን።"

መዝ   ፻፴፪ ÷ ፯ - ፰

ሰኔ 20 -21
ቤተክርስቲያን የታነፀችበት
282 views03:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ