በትግራይ #ኔትዎርክ ተቋርጧል። በትግራይ ክልል ከምሽት 12 ሰዓት አንስቶ የኔትዎርክ አገልግሎት መቋረጡን በዚህም ምክንያት " ምን ተፈጥሮ ነው ? " በሚል ጭንቀት እንደገባቸው የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ገልጸዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቤተሰቡን አባላት መልዕክት ይዞ ኢትዮ ቴሌኮምን አነጋግሯል። ኢትዮ ቴሌኮም ፤ እውነት ነው ኔትዎርክ ተቋርጧል ሲል አረጋግጦልናል። " ኔትዎርክ የተቋረጠው ፋይበር ተቆርጦ " ነው ያለው ኢትዮ ቴሌኮም " ሰራተኞቻችን በጥገና ላይ ናቸው " ብሏል። " ከማዕከል የሚያገናኘው ፋይበር ሁለት ቦታ ተቆርጧል፤ ዋናው እና የመጠባበቂያውን ጨምሮ " ያለው ኢትዮ ቴሌኮም ፤ ከመቐለ ፣ ከደሴ እና ከሰመራ ሰራተኞች ተሰማርተው በርብርብ እየሰሩ ይገኛሉ ሲል አሳውቋል። የጉዳቱን መጠን በተመለከተ ላቀረብነው ጥያቄ " ምሽት በመሆኑ የጉዳቱን መጠን ማረጋግጥ አልተቻለም " ተብለናል። @EBS_TV_NEWS 486 views03:26