Get Mystery Box with random crypto!

#ባጃጅ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች / ባጃጅ መታገዱን | EBS TV NEWS

#ባጃጅ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች / ባጃጅ መታገዱን በተመለከተ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አጭር ማብራሪያ ሰጥቷል።

በማብራሪያው ፤ " መንግስት የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችን #የነዳጅ_ድጎማ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረጉ እየታወቀ የባለሶስት ጎማ ወይም በተለምዶ አጠራራቸው የባጃጅ አሽከርካሪዎች ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ እንዲሁም የተወሰኑት በወንጀል ድርጊቶች ላይ በመሰማራት የከተማችን ነዋሪ የቅሬታ ምንጭ ሆነዋል " ብሏል።

የከተማ አስተዳደሩ የባጃጅ አገልግሎትን ስርዓት ለማስያዝ የአሰራር ማስተካከያ እያደረገ መሆኑን ገልጾ ይህ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ በከተማድ ሁሉም አካባቢዎች የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት #እንዲቆም መወሰኑን ገልጿል።

የተሸርካሪዎቹ ከስራ መውጣት በነዋሪው ላይ የትራንስፖርት ጫና እንዳያሳድር አስተዳደሩ ሌሎቹ የትራንስፖርት አገልግሎቶች በሙሉ አቅማቸውና በቅንጅት አገልግሎት የሚሰጡበትን ሁኔታ መመቻቸቱን አመላክቷል።

(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሌሎች ጉዳዮችንም ያነሳበት የዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@EBS_TV_NEWS