' ሰላተል ኢስትስቃ '
ነገ በመላ ሀገሪቱ "ሰላተል ኢስ ትስቃ" እንዲሰገድ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ጥሪ አቅርቧል።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቦረና ዞን በዝናብ እጥረት ምክንያት የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ በመላ ሀገሪቱ " ሰላተል ኢስ ትስቃ " እንዲሰገድ ለመላው ምዕመን ጥሪ አድርጓል።
ነገ ሰኞ በመላው ሀገሪቱ እንዲሰገድ ጥሪ የቀረበው " ሰላተል ኢስትስቃ " ዝናብ በሚርቅበት ጊዜ የሚሰገድ ሰላት መሆኑን ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
በሌላ በኩል ፤ ጠቅላይ ም/ቤቱ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን ዕርዳታ የሚውል ድጋፍ ማሰባሰቢያ የባንክ ቁጥሮችን ይፋ አድርጎ ድጋፍ እያሰባሰበ እንደሆነ ተሰምቷል።
ጠቅላይ ም/ቤቱ ይፋ ያደረጋቸው የባንክ ቁጥሮች ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሣብ ቁጥር 5582 ፣ ዳሸን ባንክ ሂሣብ ቁጥር 795571270973፣ ዘምዘም ባንክ ሂሣብ ቁጥር 222255፣ ሂጅራ ባንክ ሂሣብ ቁጥር 308010 ፣ ኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ቁጥር 1000093406226 ናቸው።
@EBS_TV_NEWS