2022-07-10 06:25:00
ማህበራዊ ሚዲያ ተቀላቀልኩ ጊዜው አጭር አይደለም። ነገር ግን አጠቃቀሙን ብዙም አይደለሁም።
ለዚህም መሰለኝ ብዙ ተከታይ የሌለኝ።
ተከታይ ያለመኖሩ ያለመብዛቱ like share comment የሚያደርግ ሰው ቁጥር እጅግም አያስጨንቀኝም።
ነገር ግን ሁሌም የሚያስጨንቀኝ ዛሬ ለራሴ ምን ጥሩ ነገር ልንገረው የሚለው ነገር ነው፤
ነገ ሰወች ወደ ሕይወቴ፣ አካውንቴ፣ መልዕክቴ ሲመጡ አያፍሩም፤ ሁሉ ሙሉ ሁሉ ዝግጁ ነውና።
ከፌስቡክ፣ ወደ ትዊተር፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክ፣ ከዛም ወደ ኢንስታግራም እየተቀላቀልኩ መጣሁ። አሁንም ሰወች ወደኔ አልመጡም፥ አንድ የገባኝ ነገር እኔ የጎደለብኝ ነገር ሳይኖር እነርሱ የፈጠርኩላቸውን እድል አለመጠቀማቸው ነው የሚታየኝ።
በእርግጥ ወደኔ ከሚመጡት የማገኘው ነገር ቢኖርም እኔ ግን የማውቀው ያጣሁት ነገር የለም። ያልመጡት ግን የተዘጋጀላቸውን አጥተዋልና። እኔ ግን ለቤቴ ለሕይወቴ ለአካውንቴ ለተከታዮቼ የሚሆነውን የሚመጥነውን ዛሬም አስባለሁ፣ አዘጋጃለሁ፣ እለጥፋለሁ።
ለሚመጡት እድል እየፈጠርኩ እንደሆነ ይሰማኛል።
ልዩነት እየፈጠርኩም እንደሆነ አምናለሁ።
አንድም ሰው እዚህ ገጽ ላይ ገብቶ አንዱንም አይረባም እንደማይል አምናለሁ። አንዱን ከአንዱ ያበላልጥ እንደሆነ እንጂ። የተከታዮቼን ማነስ አይቶ ይንቀኝ እንደሆነ እንጂ የተለጠፉትን አይቶ አንዳችም እንከን አያወጣልኝም።
ለምን?
ለዛሬ አልሰራም።
ለነገ እንጂ። ትውልድ የሚረከብ፣ ትውልድ የሚያሸጋግር ስራ ነውና የምሰራው።
ኑ ወደ ጓዳዬ ዝለቁ ከመአዴም ተቋደሱ። ደስም ይበላችሁ። ነፍሳችሁም ትርካ ስጋችሁም ይረፍ። አዕምሯችሁ እንዲህም አለንዴ ብሎ ይደነቅ፤ ያድንቅ።
@t.me/deressereta
51 viewsEagel view R.E, 03:25