Get Mystery Box with random crypto!

Development Bank of Ethiopia (DBE) : Training to Lease Financing

የቴሌግራም ቻናል አርማ dbetraining2014 — Development Bank of Ethiopia (DBE) : Training to Lease Financing D
የቴሌግራም ቻናል አርማ dbetraining2014 — Development Bank of Ethiopia (DBE) : Training to Lease Financing
የሰርጥ አድራሻ: @dbetraining2014
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.61K
የሰርጥ መግለጫ

New and current information specifically about SMEs training, eligibility for the lease financing, documents required by DBE for this service, and other relevant issues are addressed through this channel.

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-08 09:27:54
19.8K views06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-08 09:27:35
19.6K views06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-08 09:26:14 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ባወጣው ክፍት የስራ ቦታ ለመወዳደር የትምህርትና የስራ ልምድ አሟልተው ነገር ግን የተቀመጠውን የእድሜ ገደብ፣ የመቼ ዓ.ም ምሩቅ፣ ስንት የመመረቂያ ነጥብ የያዙ እና ሌሎች መሰል ጉዳዮችን አስመልክቶ ስለጉዳዩ ካለማወቅ አንዳንድ አመልካቾች የተቀመጡትን መስፈርቶች ባያሟሉም እንደሚያመለክቱ አመላካቾች ታይተዋል፡፡
በመሆኑም፣ ባንኩ ላወጣው ክፍት የስራ ቦታ ለማመልከት የሚሹ ሰዎች ከማመልከታችው በፊት ከስር Notes to the DBE job application የሚለውን ምስል ከፍተው መረጃውን መመልከት ይችላሉ፣ በተለይም፡-

• በጀማሪ መኮንን የሚያመለክቱ
1. እድሜያቸው ከ30 መብለጥ የለበትም
2. በ2020 ወይም ከዛ ወዲህ የተመረቁ መሆን አለባቸው
3. የመመረቂያ ነጥባቸው 3.00 እና ከዚያ በላይ መሆን ይኖርበታል

• አንድ አመልካች ማመልከት የሚችለው በ2 የስራ መደቦች ላይ ብቻ ነው
• ሙሉውን ከምስሎቹ ይመልከቱ

የማመልከቻው አድራሻ https://jobs.dbe.com.et/
18.8K views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 16:24:24 አዲስ ዜና

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ4ኛ ዙር አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠናን ሁሉንም የስልጠና ቀናት ሳያቆራርጡ ያጠናቀቁ ሰልጣኞች የቢዝነስ የአዋጭነት ምክረ ሀሳባቸውን እንዲያስገቡ ጥሪ አቀረበ፡፡

ባንኩ ከወራት በፊት በ4ኛ ዙር የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና 112 ሺህ ለሚሆኑ ስራ ፈጣሪዎች ስልጠና መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ከሰልጣኞች መካከል አምስቱንም ቀናት ስልጠናውን የተከታተሉና ሰልጠነው ያጠናቀቁ ለምስክር ወረቀት ዝግጁ የሆኑ ሰልጣኖች ብቻ ወደ ባንኩ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች በመቅረብ ሪፖርት እንዲያደርጉና የቢዝነስ አዋጭነት ሀሳባቸውን እንዲያስገቡ ነው ባንኩ ያሳሰበው፡፡

ሙሉ በሙሉ ስልጠናውን ተከታትለው ለአጠናቀቁ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት የማዘጋጀቱ ስራ እየተሰራ ሲሆን፣ የሰልጣኞችን የስራ ጊዜ በአግባቡ ለመጠቀም ሲባል ቀሪ የሌለባቸው ሰልጣኞች የቅድመ ዝግጅት ስራቸውን እንዲጀምሩ ነው ባንኩ ሁኔታዎችን ያመቻችው፡፡

ሰልጣኞች ወደ አምራች ኢንዱትሪ ዘርፍ ለመግባት ያላቸውን የስራ ተነሳሽነት ባንኩ መደገፍና ማበረታታት ስላለበት የስልጠና የምስክር ወረቀቱ እስኪሰራጭ ድረስ በልዩ ሁኔታ ማስታናገድ እንደሚገባ ስለታመነበት ነው፡፡

በዚህም መሰረት ሙሉ በሙሉ ሁሉንም የስልጠና ቀናት ሳያቆራርጡ የሰለጠኑ ሰልጣኞች እድሉን በመጠቀም ወደ ተመዘገቡባቸው የባንኩ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች በመቅረብ በተመቻቸው እድል እንዲጠቀሙ ባንኩ ጥሪ አቅርቧል፡፡
18.7K views13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 14:27:09 ማስታወሻ

የ 4ኘው ዙር ስልጠና ተመዝጋቢዎች ሆነው በአንደኛው ምእራፍ/ዙር ያልተጠሩ ሰልጣኞች መኖራቸውን፣ ስለዚህ በቀጣይ በሌሎች 2 ምእራፎች የተቀሩት ተመዝጋቢዎች ጥሪ እንደሚደረግ መነገሩ ይታወቃል።

ሆኖም ግን አንዳንድ ተመዝጋቢዎች ስልኬ ስለማይሰራ ስለነበር፣ ከሀገር ውጪ ስለነበርኩ፣ እና በመሰል ምክንያቶች ለ1ኛው ዙር/ምእራፍ ተጠርተው ከነበር ለማረጋገጥ አሁንም ድረስ በቅርንጫፍ ቢሮዎች እየቀረቡ እየጠየቁ መሆኑንና እነርሱ የሚያውቋቸው ለመጀመሪያው ምእራፍ ስልጠና ጥሪ ከተደረገላቸው ሰዎች ስልክ በመውሰድ እየደወሉ ለማረጋገጥ እየሞከሩ እንደሆነ ተስተውሏል። ስለዚህ ለመጀመሪያው ምእራፍ/ዙር ስልጠና የተጠሩ ሰልጣኞች ስም እስካሁን ያልደረሳችሁና መሰል ጥያቄ ያላችሁ ከ https://www.dbe.com.et/ ድረ ገፅ ላይ እንድትመለከቱት እንጋብዛለን።

የ4ኛው ዙር ተመዝጋቢዎች ቀጣይ ምእራፍ ስልጠና መቼ ነው የሚለው የአብዛኛዎቹ ጥያቄ መሆኑ በተግባር ከሚቀርቡ ተመዝጋቢዎች ጥያቄ ማውቅ ተችሏል።

ይህ ጥሪ መቼ ተደርጎ ስልጠናው ይሰጣል የሚለውን ባንኩ ባሉት የሚዲያ አማራጮች የሚያስታውቅ የሚያስታውቅ ስለሆነ በትእግስት እንድትጠብቁ እንጠይቃለን።

እንዲሁም ይህንን ስልጠና የወሰዳችሁ የምስክር ወረቀት ስለመዘጋጀቱ ለማወቅና ለመውሰድ እየጠየቃችሁ መሆኑ ታይቷል። ስለዚህ የምስክር ወረቀታችሁ ተዘጋጅቶ እንዳለቀ ባንኩ የሚያሳውቅ ስለሆነ አሁንም በትዕግስት እንድትጠብቁ እንጠይቃለን።

አንዳንዶች ባለማወቅ በአካል እየመጡ በአክስዮን ሰልጣኞችን እንድናደራጅ ባንኩ ፍቃድ/እውቅና ይስጠን የሚል ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑ ታይቷል።

በአክስዮን መደራጀትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፍላጎቱ ያላቸውና መስፈርቱን የሚያሟሉ ዕጩዎችን እንዲደራጁ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለፀ እንጂ ለማንም አካል በአክስዮን የማደራጀት ስራ እንዲሰራ ወይም እንዲሰራለት እውቅና እሰጣለሁ ወይም እፈቅዳለው ብሎ ያስተላለፈው መልዕክት የለም።

ስለዚህ፣ ሰልጣኞችን በአክስዪን እናደራጅ የሚል ጥየቄ እያቀረቡ ያሉ ሰዎች ባንኩ ከሚመራበት ፓሊሲና እና ፕሬዚደንቱ በስልጠና ማእከላት ከተናገሩትና እና በሚዲያ ከሰጡት ማብራሪያዎች መረዳት ያለባቸው ማመልከት የሚሹ ሰልጣኞች/አመልካቾች በሚፈልጉት ፕሮጀክት ዙሪያ ተሰባስበው፣ የአክስዮን ህግን እና አሰራርን ጠብቀውና አሟልተው ሲገኙ ባንኩ ያደራጃቸውና ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋል የሚለውን ነው። ባንኩ ለማንም አካል የማደራጀት እውቅና እሰጣለው አለማለቱን መገንዘብ ያስፈልጋል።
13.2K views11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 16:39:41 ማሳሰቢያ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአክሲዮን ለማደራጀት ፈቃድ የሰጠው አካል የለም!

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሰቃሾች ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ በማስገባት ላይ ላይ መሆኑን ተከትሎ በአንዳንድ አካላት ተቋሙን የማይወክሉ የተሳሳቱ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶችም ሆነ የአክሲዮን ማደራጀት ስራውን ባንካችን በራሱ አሰራር መሰረት የሚፈጽም እንጂ ሌላ ተቋም እንዲሰራለት ውክልና አልሰጠም።

በመሆኑም የአክስዮን አደረጃጀትን ጨምሮ ሌሎች ባንኩ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ከባንካችን ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን እና ዌብሳይታችን ላይ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

በመሆኑም ከዚህ በታች የተያያዘውን መረጃ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከቱ ዜናዎች ከባንካችን ፈቃድ አግኝተው እየሰሩ አለመሆናቸውን እንድትረዱ እናሳስባለን።

ከሰሞኑ አንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እየሰጠ ያለውን ስልጠና እንደ መልካም አጋጣሚያቸው ተጠቅመው በአክሲዮን የመደራጀት መልካም እድል እንደተፈጠረላቸው በማስመሰል መኪናን ጨምሮ በወር እስከ 60,000 ብር የሚደርስ ገቢ የሚያስገኝ ስራ እንዳላቸው፣የትርፋማ አክስዮን ድርሻ ባለቤት፣የኤሌክትሪክ መኪና እንደሚያገኙ፣የልማት ባንክ ብድር እንደሚያመቻቹ በመግለፅ ቴሌግራምን ጨምሮ በተለያዩ የማህበራዊ የትስስር ገፆች ላይ በማስተዋወቅ ላይ ይገኛሉ።

በመሆኑም የባንካችንን ስም በመጠቀም እናደራጃለን፣ ብድር እናሰጣለን በሚል የትኛውም አካል የሚያሰራጨው መረጃ ህገወጥ የወንጀል ድርጊት መሆኑን እንድታውቁና እንዳትጭበረበሩ እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአክሲዮን ተደራጅቶ ለመምጣት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችንና ሌሎች አስፈላጊ ሂደቶችን በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገፆቻችን የምናሳውቅ ይሆናል፡፡

ተመሳሳይ ጥቆማዎችን ለባንካችን በማድረስ ሃሰተኞችን እንድታጋልጡ እየጠየቅን መሰል የማጭበርበር ድርጊቶችን በሚከተሉት ቁጥሮች እንድታሳውቁን በዚህ አጋጣሚ እንገልፃለን፡፡

1. 0904374444 ወይም
2.  0904357735 ወይም
3.  0904364436
23.6K viewsedited  13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 12:43:07 ክፍል አራት






ክፍል አምስት



30.9K views09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 18:55:31 በቀጥታ በዩትዮብ ለመከታተል ለምትፈልጉ

Part one






Part two





Part three



30.3K views15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 18:29:24
የአባ መላ ሙሉ ቪዲዮ ክፍል አንድ
26.4K views15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 11:43:56 Development Bank of Ethiopia (DBE) : Training to Lease Financing pinned a file
08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ