2022-06-28 20:59:19
ሁለት ነጥብ
~
1- ከጥቂት አመታት በፊት ሸይኽ ሙሐመድ ባ ሙሳ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ነበር። ያኔ በመጡበት ጊዜ ከሳቸው ጋር እንደተገናኘሁ አድርጎ ስሜን ጠቅሶ የፃፈ ሰው አይቻለሁ። እኔ ሸይኽ ሙሐመድ ባ ሙሳን በተባለው ጊዜም፣ ከዚያ በፊትም፣ ከዚያ በኋላም በአካል አግኝቻቸው አላውቅም።
ለመጀመሪያ ጊዜ ባለፈው ሚያዚያ 30 በዋትሳፕ የድምፅ መልእክት ከላኩልኝ በኋላ ትንሽ አውርተናል። ይሄ ደግሞ ገና ሁለት ወር እንኳን አልሞላውም። ከዚያ በፊት በአካል ቀርቶ በስልክም በኢንተርኔትም ከሳቸው ጋር የድምፅም የፅሁፍ መልእክት ተለዋውጨ አላውቅም። ስለዚህ የተወራው ነገር ሙሉ በሙሉ ውሸት ነው።
2- ባለፈው አመት ኮምቦልቻ በነበረው ደውራ ላይ አንድ ጤነኛ ያልሆነ ሰው ከሳዑዲ በስልክ እንዲያስተምር እኛ እንዳመቻቸን አድርጎ ፅፏል አንድ ወንድም። ይህም ውሽት ነው።
የተባለው ሸይኽ ዓዲል አሱበይዒ የሚባል ሲሆን እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ስሙን የሰማሁት የዚያን ቀን ነው። በእለቱ ለጠየቀኝም ሰው ስለ ሸይኹ የማውቀው ነገር እንደሌለ፣ እንዲቀርብ ያደረግሁትም እኔ እንዳልሆንሁ ተናግሬያለሁ። ዛሬም ድረስ የተጠቀሰውን ሸይኽ በተመለከተ ከስሙ ባለፈ ክፉም ደግም አላውቅም። እንዲያስተምር የተመቻቸው በጦሀ ኸዲር በኩል እንደሆነ ብቻ ሰምቻለሁ። አለቀ።
-
ነገሮቹ ዘለግ ካለ ውንጀላ ጋር የቀረቡ እንደመሆናቸው ሰፋ ያለ ምላሽ የሚፈልጉ እንደሆኑ ባምንም ከዚህ በላይ ማለት አልሻም። ምክንያቱም:-
1ኛ፦ በብዙ ነገሮች ላይ ለራሴ ዝምታን እንደ አቋም መርጫለሁ። በትንሽ በትልቁ ከራሴ በመከላከል ላይ ተጠምጄ ሌሎችን ቢዚ ማድረግ አልፈልግም። ይቺን የጫርኩትም ከተለያዩ ወንድሞች ወቀሳ ሲመጣብኝ ነው። ወደፊትም ቢሆን ለየትኛውም ውንጀላ ምላሽ የመስጠት ፍላጎት የለኝም። አስገዳጅ ሲሆን ብቻ ልክ እንደዚህ ወደ ውስጥ ሳልገባ በስሱ ብቻ ነካ ላደርግ እችላለሁ፣ ምናልባት። ለጊዜው ከብዙ አቅጣጫ ካሰላሰልኩ በኋላ የደረስኩበት ውሳኔ ይሄ ነው።
2ኛ፦ ከላይ እንደጠቆምኩት በቅርቡ ሸይኽ ባ ሙሳ የዋትሳፕ መልእክት ከላኩልኝ በኋላ በመጠኑ ተነጋግረናል። ከሳቸው በኩል የቀረበው አደራ ነገሩን በማረገብ በኩል የበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ የሚያሳስብ ነው። ለዚህም አደራ ዋጋ እሰጣለሁ ኢንሻአላህ።
=
https://t.me/IbnuMunewor
308 viewsⒶbu Fewzan iftah, 17:59