የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባዘጋጃቸው 10ኛው ዙር “ይቆጥቡ፣ ይሸለሙ” እንዲሁም 21ኛ፣ 22ኛ እና 23ኛ ዙሮች “ይቀበሉ፤ ይመንዝሩ፤ ይሸለሙ!” መርሃ-ግብሮች ተሳታፊ በመሆን እደለኛ መሆን የቻሉ ደንበኞች ዛሬ ነሀሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም የብሄራዊ ባንክ ገዢ የተከበሩ ዶ/ር ይናገር ደሴ፣ የብሄራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ፍቃዱ ድጋፌ፣ የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ገረመው ጋርጄ፣ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ የባንኩ የሥራ ኃላፊዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ሥነ-ስርዓት ሽልማታቸውን ተረክበዋል፡፡ 378 views11:19