Get Mystery Box with random crypto!

የሚጣፍጥ ስቃይ ተከታታይ ልብወለድ በያኔት ማስረሻ ክፍል ፲፩ @yanetmasra | Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር

የሚጣፍጥ ስቃይ

ተከታታይ ልብወለድ
በያኔት ማስረሻ
ክፍል ፲፩
@yanetmasra

ወይ በሱፍቃድ እሱን መች አጣሁት መቼም ፈርተህ ኢየሱስን  እንድትክደው አልመክርህም ግን ቢያንስ ከእነሱ ጋር መመላለሱን አቁም ሲጠይቁህ ግን መልስላቸው እይታ ውስጥ  አትግባ መናገር ካለብህ ነገር በላይ አትናገር የኔ ሀሳብ ይሄ ነው በተረፈ የወደድከከውን አድርግ አልኩት እኔ እዛው ጭ  እንዳልኩ የእናቴን  ጥሪ ድምፅ ሰምቼ ለመውጣት ከመቀመጫዬ ተነሷው እሷ ከእኔ ቀርባ ኖሯል  ገና ሳልወጣ ገባች " አንተ ፈጣሪ የረገመህ ልጅ ጠፋብኝ ብዬ ሀገር ለሀገር ሳስ አንተ እንደ አይጥ እዚህ ተወሽቀህ ኖሯል ምናለ ስትወጣ እየተከተልኩህ መሆኑን አውቀሀል መለስ ብለህ እንኳን  እናቴ የት ገባች  አትልም ደሞ እዚህ ምን ትሰራለክ ጭራሽ እዚህ መዋል ጀመርክ እንደአለቺኝ  እውነት ለመናገር ከሆነ ሀሳቤ በሱፍቃድ ላይ ሆኖ  እናቴ ምንም ትዝ አላለቺኝም ነበር "ወይ እማ በጣም ጎድተውት ስለነበር ከእናቱ ጋር ደግፈን  እቤት አመጣነው በዚህ ሁኔታ ላይ ሆኖ አንቺ ምንም ትዝ ልትይኝ አልቻልሽም ለዛ ነው ይቅርታ እንጂ ለመዋልም ፈልጌ አልነበረም አልኳት ይመስለኛል እናቴ ቤታቸው ያለዛሬ ገብቼ የማውቅ አልመሰላትም ብታውቅ ደስ ስለማይላት ዛሬ ገና እንደገባው አስመሰልኩ እንጂ በጣም ቤታቸው ከመግባቴ የተነሳ ቤታቸው ቤቴ እየመሰለኝ መቷል የበሱፍቃድ አባት የቤተክርስቲያን አገልጋይ ናቸው መፅሀፍ ቅዱስን ያስተምራሉ በዚህ ምክነያት ህይወታቸው ቀላል የሚባል አልሆነም እንዲያውም በሱፍቃድ እንደነገረኝ ከሆነ  የበፊት ቤታቸውን ለቀው የወጡበት ሠፈርተኛው ስለሚጠሏቸውና  በእነሱ ላይ የሚሰሩት ደባ መቋቋም ስላቃታቸው መሆኑን ነግሮኛል በል አሁን ቀጥ ብለህ ውጣ እዚህ ስትርመጠመጥ ደሞ ትታይና ሌላ እዳ እንዳታመጣብኝ



እንግዲህ ብመክር ብዘክርህ ባጥንህ አልሰማ ብለኸኛል አባትህ ሲመጣ ሁሉንም  ነግሬ የሚያደርግህን ያደርግሃል ቢገልህም አልራራልህም ሆ ሆ ያኔ  በእንቁላሉ ጊዜ በቀጣሺኝ እንዳይመጣ ከአሁኑ ብቀጣህ ይሻላል አለቺኝ በእርግጠኝነት አባቴ ሲመጣ እንደምትናገረው አልጠራጠርም አባቴን በጣም ነው የምፈራው እንኳን ሊገርፈኝ አይደለም ቀና ብዬ  ፊቱን ሳየው ራሱ ከመደንገጤ የተነሳ ልቤ ትርክክ ይላል እንደውም ከእኔ ይልቅ ለታናናሽ እህቶቼ ፊቱ ይፈታል አንዳንዴም ሸነጥ ካደረገው ሊያጫውታቸው ይችላል  ታዲያ ይህን ባለችን በሳምንቱ አንድ መጥፎ ዜና ይናፈስ ጀመረ ከአባቴ ጋር የነበሩ ብዙ ወታደሮች ህይወታቸው ማለፉን እና ለቤተቦቻቸው መርዶ መነገሩ ገሀድ ሆነ ታዲያ የአባቴ ድምፅ መጥፍቱ  ደብዳቤም  እየላከ ባለመሆኑ እናቴ ስጋት እየገባት መጥቷል እኔም ብሆን ፍቅሩን ያላጣጣምኩት በውል ማንነቱን ያልተረዳሁት አባቴ ነገር እያሳሰበኝ መጣ ጎረቤቶቻችን አንዳንድ እየመጣ ያፅፅናል አንዳንድ የሚናገረውን የማያውቅ ደሞ ጭራሽ ሆድ ያስብሰናል ግን የፈሩት ይደረሳል እንደሚባለው ሁሉ አንድ ቀን እየነጋጋ ሳለ ቤታችን ተንኳኳ እናቴ "ማነው ?" እያለች በሩን ለመክፈት ተጠጋች ፊቷ ግን ተረብሾ ነበር ልክ ስትከፍተው ብቻ ሰዎቹ  አንድ ነገር ሳይናገሩ ጭንቅላቷን ይዛ እዬዬዋን ቀጠለች "ወይኔ! ጀግናው ወይኔ ! ወንዱ የልጆቼ አባት የልጅነቴ እኔ አፈር ልብላልህ እኔ እንደወጣሁ ልቅር  ልጆችህን በትነህ እኔን ለማን ጥለህ ትሄዳለህ ........ በጣም አለቀሰች ድንጋጤዬ ካለሁበት አላንቀሳቀሰኝም አይኖቼ እናቴ ላይ ፈጠው ቀሩ እሷን ለማረጋጋት ለያረዱ የመጡ ሰዎች ባንድ በኩል ያለቅሳሉ በሌላ በኩል ያፅናኗታል ብቻ ሆነም ቀረ የአባቴ መሞት እውን ሆነ ቤተዘመዶች ቢሰበሰቡ ....ይቀጥላል


ለሌሎችም እንዲደርስ #share


     ይ ላ ሉን
@christian_mezmur
@christian_mezmur