ሚሼል ባሽሌት ግጭት እንዲቆም ተማፀኑ። የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሼል ባቼሌት በሰጡት መግለጫ በሰሜን #ኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል። " ሲቪሎች በቂ ጉዳት ደርሶባቸዋል " ያሉት ባሽሌት አሁን ዳግም ግጭት መቀስቀሱ አስፈላጊ የሆነ ድጋፍ የሚሹ የሰላማዊ ዜጎችን ስቃይ የሚያባብስ ብቻ ነው ብለዋል። ባሽሌት ፤ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት (TPLF) አሁን ያለውን ሁኔታ ለማርገብ እንዲሰሩና ግጭቱን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ ተማፅነዋል። @BreakingNewsEthiopiaa 2.2K views20:46