Get Mystery Box with random crypto!

ቤተክርስቲያን ከውስጥም ከውጭም ብዙ ፈተና አለባት። ለምሳሌ እንዚህ ሽማግሌዎች ራሳቸውን በራሳቸው | በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

ቤተክርስቲያን ከውስጥም ከውጭም ብዙ ፈተና አለባት። ለምሳሌ እንዚህ ሽማግሌዎች ራሳቸውን በራሳቸው ያጰጰሱና ያፐተረኩ ሰዎች ናቸው። የቅባቶች ጳጳስ ነን ባይ ናቸው። ፓትርያርኩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ነው የምባል ነው የሚሉት። ቅባት ችግሩ የዶግማ ነው። በጠቅላላው ተወግዞ መለየት ሲገባው እያጭበረበረ ቤተክርስቲያን ውስጥ እንዲኖር ዝም ተብሏል። ቤተክርስቲያንን ከውስጥ ሙሰኛው፣ ሌባው፣ ጎጠኛው፣ ሹመት ወዳጁ፣ ተሐድሶው ወዘተ ለመጣል ይታገላል። ከውጭም ብዙ ፈተና አለባት።

ነገር ግን ይህ ሁሉ ቢሆንም የተመሠረተችው በክርስቶስ መሠረትነት ስለሆነ ሁሉንም ታልፈዋለች። ሰይፍን የተመረኮዙ ሰዎች ራሳቸው ይጎዳሉ። ጥቂት የዋሃንንም ሊጎዱ ይችላሉ። ከዚህ መናገር ያስፈለገው የዋሃንን ማትረፍ ከተቻለ በሚል ነው እንጂ አውቀው ያበዱትን ለመመለስ አይደለም። አውቆ ያበደ አይመለስምና።

የቅባት አስተምህሮ ከሐዋርያትና ከቅዱሳን ሊቃውንት አስተምህሮ የተለየ ስለሆን የሐዋርያትን ዶግማና ቀኖና አይጠብቅም። ለዚያ ነው በጉልበት በራሳቸው ፈቃድ ተነሣስተው ጰጰስን ፐተረክን ያሉት። በሐዋርያት እና በሠለስቱ ምእት ቀኖና ደግሞ አንድ ሰው ጳጳስ የሚሆነው ፓትርያርኩ ፈቅደው ቢያንስ ሁለት ወይም ሦስት ኤጲስ ቆጶሳት ሹመውት ነበር። እኒህ ወንበዴዎች ግን በግላችን ጰጰስን አሉልሀ። ዲቁና እና ቅስናም እየሾሙ እንደሆነ ሰማሁ። ምነው ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲህ ዓይነት ቀበሮዎችን ዝም አለ???

ይህ ቆብ ግን ምነው ፈላጊው በዛሳ!!