"ጸጋ ነሣእነ ወሕይወተ ረከብነ በኃይለ ጸሎቱ ለያሬድ አቡነ። ኪያከ ነአኵት ነሢአነ ጸጋ ዘእመንፈስ ቅዱስ"
።
የሰው ልጅ የተፈጠረው እግዚአብሔርን እያመሰገነ በክብር ላይ ክብር እየተጨመረው ይኖር ዘንድ ነው። ሰው እግዚአብሔርን በማመስገኑ ራሱ ሰው ይጠቀማል እንጂ ለእግዚአብሔር ያሚጨምርለት ነገር የለም። እርሱ በባሕርይው ምስጉን ነውና።
።
ኑ ካለመኖር በቸርነቱ የፈጠረንን እግዚአብሔርን እናመስግነው።
።
ኑ ክረምትና በጋን፣ መዓልትና ሌሊትን እያፈራረቀ ምድር እንድታበቅል እያደረገ የሚመግበንን የሚያኖረንን እግዚአብሔርን እናመስግነው።
።
ኑ ብንበድል መመለሻ ንስሓን የሰጠን፣ ከሕይወት ብንራቆት እንታደስ ዘንድ ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ ብሎ የሰጠንን እግዚአብሔርን እናመስግነው።
።
ኑ ስለእኛ በመስቀል ተሰቅሎ ያዳነንን ኢየሱስ ክርስቶስን እናመስግነው።
።
በእውነት ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል።
እንኳን አደረሳችሁ።