Get Mystery Box with random crypto!

__የሐዋርያት ሲኖዶስ ክፍል ፬__ #ትእዛዝ #ሲኖዶስ ትእዛዝ ፳:- ኤጲስ ቆጶ | በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

__የሐዋርያት ሲኖዶስ ክፍል ፬__
#ትእዛዝ #ሲኖዶስ
ትእዛዝ ፳:- ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ወይም ዲያቆን መማለጃ በመስጠት የሹመት መዓርግ ቢይዝ ይሻር። የሾመውም ይሻር። ከክህነት ሥርዓትም እስከ መጨረሻው ይባረር።

ትእዛዝ ፳፩:- ኤጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያንን በዚህ ዓለም የአገዛዝ ሥርዓት ለመግዛት የሚፈልግን ሰው ከረዳ ይሻር።

ትእዛዝ ፳፪:- ቄስ ኤጲስ ቆጶስን ቢንቅ ይለይ።

ትእዛዝ ፳፫:- ኤጲስ ቆጶስ ያባረረውን ቄስ ወይም ዲያቆን ራሱ ካልፈቀደ በስተቀር ሌላ ኤጲስ ቆጶስ እንዲመለስ አያድርገው።

ትእዛዝ ፳፬:- ሊቀ ጳጳሳት የሁሉንም ሀገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶሳት ያውቅ ዘንድ ይገባል።

ትእዛዝ ፳፭:- ኤጲስ ቆጶስ የሀገረ ስብከቱ ኤጲስ ቆጶስ ካልፈቀደለት የእርሱ ባልሆነ ሀገረ ስብከት ላይ ለመሾም አይደፋፈር። ተደፋፍሮ የተገኘ ካለ እርሱም የሾማቸውም ይሻሩ።

ትእዛዝ ፳፯:- የኤጲስ ቆጶሳት ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይደረግ። በቤተክርስቲያን ላይ ስለአለ ስሕተትና እንቅፋት ስለሚሆኑ ነገሮችም ይተርጕሙ። የመጀመሪያው ጉባኤ በበዓለ ኃምሳ መካከል ይሁን። ሁለተኛው ጉባኤ ጥቅምት 12 ይሁን።

ትእዛዝ ፳፰:- ኤጲስ ቆጶስ የእግዚአብሔርን ገንዘብ ለዘመዱ ልጆች መስጠት የለበትም።

ትእዛዝ ፳፱:- ከቀሳውስት ወይም ከዲያቆናት ማንም ኤጲስ ቆጶሱን ሳያማክር ምንም አያድርግ።

ትእዛዝ ፴፩ [የጦር ሠራዊት]:- የንጉሥ ሠራዊትም ከጠላት ጋር ጦርነት የሚያደርጉት በራሳቸው ምግብ አይደለም።

ትእዛዝ ፴፪:- ወደ ጭፈራ ቤት የሚሔድና የሚዞር ስካርም የሚያበዛ ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ወይም ዲያቆን ይተው። አልተውም ካለ ግን ይባረር። ሕዝባውያንም ቢሆኑ እንደዚሁ ይሁኑ።

ትእዛዝ ፴፫:- ወደ ከኃድያን ጥምቀት ወይም ወደ ቁርባናቸው የሚሔድ ካህን ይሻር።

ትእዛዝ ፴፬:- ሥጋ መብላት፣ ጋብቻ፣ ወይን መጠጣት እንደ ርኩስ የሚቆጥር ቢኖር ይህን ሐሳቡን ይተው ዘንድ ይንገሩት። ካልተወ ግን ይሻር። ሕዝባዊ ቢሆንም እንዲሁ ይደረግ።

ትእዛዝ ፴፭:- ከኃጢአት ንስሓ የሚገቡትን አልቀበልም የሚል ካህን ቢኖር ይሻር።

ትእዛዝ ፴፯:- ከካህናት መካከል በገበያ የሚበላ ወይም የሚጠጣ ቢገኝ ከካህናት አንድነት ይለይ። ከካህናት መካከል አንዱ ኤጲስ ቆጶስን ቢሳደብ ይሻር። በሕዝብ ላይ በተሾመ ሰው ላይ መጥፎ ቃል አትናገር ይላልና። ቄስን ዲያቆንን የሚሳደብም ይባረር።

ትእዛዝ ፴፰:- ካህናትን ወይም ሕዝብን የሚንቅና የእግዚአብሔርን መልእክት የማያስተምር ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ይባረር። በንቀቱ ቢቀጥልበት ይሻር።

ትእዛዝ ፴፱:- ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ከካህናት የተቸገረን አይቶ ቸል ቸል ካለ የሚፈልገውን ነገርም ባይሰጠው ይለይ። በዚሁ በቸልታው ከቀጠለም ወንድሙን እንደገደለ ይቆጠራልና ይሻር።

ትእዛዝ ፵:- ከኃድያን በውሸት የጻፉትን መጽሐፍ ያሳየ ሕዝብንና ካህናትንም ለማጥመድ እንደ ቅዱሳት መጻሕፍት ቆጥሮ ወደ ቤተክርስቲያን ያስገባ ሰው ቢኖር ይሻር።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፭ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው