Get Mystery Box with random crypto!

_የሐዋርያት ሲኖዶስ ክፍል ፫____ #ትእዛዝ #ሲኖዶስ ትእዛዝ ፩:- ኤጲስ ቆጶ | በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw

_የሐዋርያት ሲኖዶስ ክፍል ፫____
#ትእዛዝ #ሲኖዶስ
ትእዛዝ ፩:- ኤጲስ ቆጶስ ሁለት ወይም ሦስት ኤጲስ ቆጶሳት በተገኙበት ይሾም። ቄስ ዲያቆንና የቀሩት ሹማምንት በአንድ ኤጲስ ቆጶስ ሥልጣን ብቻ ይሾሙ።

ትእዛዝ ፪:- ጌታችን ካዘዘው (ስንዴ፣ የወይን ፍሬ፣ መብራት፣ ዘይት፣ ንጹሕ ዕጣን) ውጭ ቁርባን ያሳረገ ይሻር።

ትእዛዝ ፫:- ካህን በአገልግሎት ምክንያት ሚስቱን አይፍታ። ከፈቱ ይለዩ። ካልመለሷት ግን ይሻሩ።

ትእዛዝ ፬:- ካህናት ቀንና ሌሊቱ እኩል ከመሆኑ በፊት ከአይሁድ ጋር ቅድስት ፋሲካ እንድትውል ካደረጉ ይሻሩ።

ትእዛዝ ፭:- ኤጲስ ቆጶስ፣ ቄስና ዲያቆን ከዚህ ዓለም ተግባር ውስጥ አይግቡ። ገብተው ከተገኙ ግን ይለዩ።

ትእዛዝ ፮:- ኤጲስ ቆጶስ ወይም ከካህናት አንዱ ምክንያቱን ሳይናገር በቅዳሴ ግን ቁርባን ባይቀበል የማይገባው ሆኖ ከተገኘ ይቅር ይበሉት። ምክንያቱን ካልተናገረ ግን ይባረር። በአሳረገው መሥዋዕት ላይም በንጽሕና እንዳላሳረገው ሆኖ ለሕዝብ እንቅፋት ሆኗልና።

ትእዛዝ ፯:- ወደ ቤተክርስቲያን የሚገባ አማኝ ሁሉ መጻሕፍትንም የሚሰማ ነገር ግን ጸሎት እስከሚያደርጉ ድረስ የማይቆም ቁርባንም የማይቀበል ከሆነ በላዩ ላይ አይጸልዩለት። ሊባረርም ይገባዋል። በቤተክርስቲያን ክርክርንና ብጥብጥን ፈጥሯልና።

ትእዛዝ ፰:- ከቤተክርስቲያን ከተባረረ ሰው ጋር አይጸልዩ።

ትእዛዝ ፲:- ካህን ከተባረረ ካህን ጋር ቢጸልይ እርሱም ይባረር።

ትእዛዝ ፲፩:- ኤጲስ ቆጶስ የሹመት ቦታውን ትቶ በሌላ ሀገረ ስብከት ሊሾም አይገባም።

ትእዛዝ ፲፪:- ያለ ኤጲስ ቆጶሱ ሥልጣን የሥራ ቦታውን ቢተውና ወደሌላ የሥራ ቦታ ቢሄድ እንዳያገለግል እኛ እናዛለን። በይበልጥም ኤጲስ ቆጶስ ወደቦታው እንዲመለስ ቢልክበትና ባይሰማው ከሹመቱ ይባረር። ባለበት ቦታ እንደ ሕዝባዊ ሆኖ ይቁረብ።

ትእዛዝ ፲፫:- ወደ ተውኔት ቤት የምትሔደውን ያገባ ክህነት ሊሾም አይገባውም።

ትእዛዝ ፲፬:- ዋስ የሚሆን ካህን ይሻር።

ትእዛዝ ፲፭:- በራሱ ፈቃድ ራሱን የሰለበ ክህነት አይሾም።

ትእዛዝ ፲፮:- በዝሙት፣ በሐሰት መማል፣ በመስረቅ የሚገኝ ካህን ይሻር።

ትእዛዝ ፲፯:- ክህነት ወደሚገቡበት ጊዜ አናጉንስጢስና መዘምራን ማግባት ቢፈልጉ ያግቡ። ከተሾሙ በኋላ ግብ ማግባት አይገባቸውም።

ትእዛዝ ፲፰:- ሰዎች ይፈሩት ዘንድ የሚደባደብ ካህን እንዲሻር እናዛለን።

ትእዛዝ ፲፱:- በታወቀ ኃጢአት ምክንያት በትክክል የተሻረ ኤጲስ ቆጶስም ቢሆን ቄስም ቢሆን ዲያቆንም ቢሆን ከተደፋፈረና ሥልጣን ባለው ጊዜ ይሠራውን የነበረውን መሥራት ከጀመረ ፈጽሞ ከቤተክርስቲያን ይራቅ።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፬ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው