Get Mystery Box with random crypto!

አትሮንስ ዘተዋህዶ-atronss zethewahdo

የቴሌግራም ቻናል አርማ atronss — አትሮንስ ዘተዋህዶ-atronss zethewahdo
የቴሌግራም ቻናል አርማ atronss — አትሮንስ ዘተዋህዶ-atronss zethewahdo
የሰርጥ አድራሻ: @atronss
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.71K
የሰርጥ መግለጫ

መፃሕፍት በዓለም ላይ ሁሉ እንደፈለግን መግባትና መውጣት እንድንችል የሚያደርጉን ቪዛ ያላቸው ፓስፖርቶች ናቸው። የየሀገሩን ወግና ልማድ ታሪክና ፍልስፍና፣ የሕዝቦችን አስተሳሰብና ባህሪ ወዘተ እንደልባችን እንድናይ እንድናውቅ የሚያደርጉን ከልካይ የሌለባቸው ዘላለማዊ ሀብቶቻችን ናቸው።
ለጥያቄዎና አስተያየትዎ @bsratbot
ለተጨማሪ ት/ት @atronss_bot
https://telegram.me/atronss

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-05 11:24:35
381 viewsኩሉ ሀብት ሠናይ ወኩሉ ፍት ኩሉ እምላዕሉ ያዕ1÷17, 08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 22:47:19 ✞ግነዩ ለእግዚአብሔር✞

ግነዩ ለእግዚአብሔር እስመ ኄር
እስመ ለዓለም ምሕረቱ እስመ ለዓለም(፪)

በዓለ ሃምሳ በሃምሳኛው በዚያች ቀን
በእሳት አምሳል ሰጣቸው ቅዱስ መንፈሱን(፪)

ሐዋርያትም ተቀበሉ ይህን ሥጦታ
እስከ ፍጻሜው በኃይል የሚያበረታታ(፪)

በብዙ ቋንቋ ሲናገሩ ተርጉመው
ጉሽ ጠጥተው ነው እያሉ አፌዙባቸው(፪)

የኢዩኤል ቃል ተፈጸመ ያ ትንቢት
ሲያፈስባቸው መንፈሱን አምላክ በዚያ ዕለት(፪)

ዞረው አስተማሩ ቅዱስ ቃሉን ትምህርት
ከክፉ አድኖ ዓለም አገኘ ሕይወት(፪)

እንግዲህ እንፍጠን ወደ እቅፍ ቤተክርስቲያን
እንድታድለን በአንድነት ቅዱስ መንፈስን(፪)

በጽርሐ ጽዮን የወረደው ቅዱስ መንፈስ
ይውረድ ይባርከን ያጽናናን ሁላችንን ይቀድስ(፪)

መዝሙር
በዲያቆን ሳሙኤል ልሳነወርቅ
3.0K viewsእናት(ነብሴ የወደደችዉን አገኘዉ እርሱም ክርስቶስ ነዉ), edited  19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 09:07:04 የማይበድል ባርያ
የማይምር ጌታ የለም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እብሉይ የተባለ በግ ጠባቂ ነበር ከኃጥያት ስራ የቀረው የለም። ያመነዝራል፣ ይሰርቃል ይገድላል በዚህም የሰይጣንን ሥራ እየፈጸመ ፵ (40) ዓመት ኖረ።

በአንዲት ዕለትም ከቀኑ እኩሌታ የመውለጃዋ ጊዜ የደረሰ እርጉዝ ሴትን አየ ሰይጣንም በልቡ ክፉ ሃሳብን ጨመረበት እንዲህም አለ ሆዷን ሰንጥቄ ህጻኑ እንዴት እንደሚተኛ ማየት አለብኝ ብሎ ጸጉሯንም ጎትቶ ከመሬት ጣላት ሆዷንም በቢላ ሰንጥቆ ልጁንም እናቱንም ገደላቸው።

በግ አርቢውም የሰራውንም ኃጥያት ተመልክቶ እጅግ አዘነ የማይበድል ባርያ የማይምር ጌታ የለም ብሎ አምርሮም እያለቀሰ ወደ በረሀ ሄዶ ፵(40) ዓመት ስለበደሉ አለቀሰ አጋንንትም ተገልጸው ከአንተ ዲያቢሎስ አባታችን ይሻላል እያሉ ያፌዙበት ነበር። እሱ ግን በተጋድሎ በረታ።

የእግዚአብሔር መልአክም ተገልጾ ስለ ሴቲቱ ደም ጌታ ይቅር ብሎሃል ስለ ልጁ ግን ይቅር አላለህም አለው አባ እብሉይም ተጨማሪ ፵ (40) ዓመት ተጋደለ ጌታም ይቅር አለው። (ስንክሳር የካቲት ፭)


ክርስቲያን ሆይ እግዚአብሔር ይቅር ባይ መሐሪ አምላክ ነው እንደ ቸርነቱ ነው እንጅ እንደኛ በደልማ በጠፋን ነበር። ስለዚህ ንስሐ ከመግባት አንቦዝን።
1.7K views ቀላያት, 06:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 12:50:41
መሰረቷ ጉልላቷ እርሱ ነው
ሙሽራዋም መስቀል ላይ የሞተው
ዛሬም ነገም ያው ነው ለዘላለም
አትንገሩን አዲስ ጌታ የለም።
1.5K views ቀላያት, edited  09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 12:04:16 ሚጡ ሥጋ ወደሙን ተቀብላ በነጠላዋ አፏን ሸፍና ስትመለስ በጓደኞቿ ላይ ብልጫዋ ተገለጠ። ኹለት ረጃጅም ሰዎች ከኋላዋ እርሷን ተከትለው ተጠምቀውና ቆርበው አፋቸውን ይዘው ተከተሏ

ምንጭ ከማህበራዊ ሚድያ የተወሰደ
1.6K views ቀላያት, 09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 12:04:16 "ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ!"
ሚጢጢዬዋ ሰባኪ

ቦታው ሐዋሳ ነው። ባለፈው ወር ከአንድም ኹለት ጊዜ ወደ ሐዋሳ ለአገልግሎት ሔጄ ነበር። ኹሌም ወደ ሐዋሳ ስሔድ አንድ አስገራሚ ነገርን መስማትን ጆሮዬ ለምዷል። ከመልመድም አልፎ ይናፍቅ ጀምሯል። ለዚያም ነው አሁን ከሐዋሳ በ25 ደቂቃ መንገድ ርቀት ተጎራብታ ወደ ምትገኘው ሻሸመኔ እየሔድኩ ይህ ታሪክ የታወሰኝ። ለነገሩ ሻሸመኔም ብዙ ታሪክ የተሠራባት ቦታ ስለሆነች ለአንድ አዲስ ድንቃይ ታሪክ ጆሮዬ ሳይቋምጥ አይቀርም።

የሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መዋዕለ ሕፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አለው። በዚህ ትምህርት ቤት ውስጥ ኦርቶዶክሳውያንም ሆኑ የሌሎች አብያተ እምነት አማኞች ይማሩበታል።

ሕፃናቱ ሰኞ ጠዋት ሲገናኙ ታዲያ የቅዳሜና እሑድ ውሏቸውን እየተሻሙ ለጓደኞቻቸው ይተርካሉ። አንዱ ከአንዷ እምቦቀቅላ አፍ ነጥቆ ያወራል፤ ሌላኛዋም እንዲሁ። ዘወትር ሰኞ ከሚተርኩት ቁምነገር መካከል ታዲያ "እኔ ትላንት ቆረብኩ" የሚለው የማይቀር ነበር። አንዷ ይህን ካለች 'እኔም' 'እኔም' የሚሉ ቀልጣፋና ኮልታፋ ኦርቶዶክሳውያን አፎች ያጅቧታል። ቁርባንን የማያውቁ ሌሎች ኮልታፎች ግራ ይገባቸዋል። ቁርባንን ከማያውቁ ኮልታፋ አፎች አንዱ የሚጡ ነው።

ሚጡ ከፕሮቴስታንት ወላጆች ተገኝታ በእናትና አባቷ ምርጫ ፕሮቴስታንት የኾነች እምቦቀቅላ ናት። ዘወትር ሰኞ ኦርቶዶክሳውያን ጓደኞቿ መቁረባቸውን በነገሯት ቁጥር ታዲያ ትቆጭ ኖሯል። አንድ ቀን ሰኞ አንዲት ሚጢጢ የክፍል ጓደኛዋ ከእናትና አባቷ ጋር አስቀድሳ መቁረቧንና በሰንበት ትምህርት ቤት የተማረችውን በመዝሙር እያጀበች ስታወራና የውሎዋን ቅድስና በመንገር እንቁልልጭ ስትል የሚጡ የመቁረብ ፍላጎት ከአቅሟ በላይ ሆነ። አንገቷን ቀለስ አድርጋ የሥረኛው ከንፈሯን እንደ ማኩረፍ ባለ መለማመጥ አሞጥሙጣ ዐይኗን በተቻለ መጠን በምስኪን አተያይ አሠልጥናና ዕምባዋም ቀሮ ወደ ቆረበችው ጓደኛዋ ሔደችና "በናትሽ እ... እኔንም እ... እ.. አቁርቢኝ" ብላ ግጥም አድርጋ ሳመቻት። ጓደኛዋ ግን "አንቺ መቁረብ አትችዪም" አለች።

"ለምን?" በሚጡ ግራ ዐይን የሞላው ዕንባ የመሬት ስበት መኖሩን አረጋገጠ።

"አንቺ ኦርቶዶክስ አይደለሽማ..."

"መቁረብ እፈልጋለሁ" ሚጡ ሊያለቅስ አምስት ጉዳይ በሆነው ድምጸት አሞሸች። ጓደኞቿ ሳቁ፤

"መቁረብ እፈልጋለሁ" ክፍሉ በሳቅ ተሞላ። ሚጡም ሳቃቸው የዐይን ሚጥሚጣ ሆነባት፤ እንባዋ ጎረፈ፤ በሳቅ የታጀበ የልቅሶ ወላፈን 'ሚስ' ባረፈደችበት ክፍል ውስጥ ተቀጣጠለ። የሚጡ ልቅሶ ካንጀት ነበርና ከሳቁ ድምቀት ይልቅ መጉላት ጀመረ። ጓደኞቿ መሳቅ ትተው ማባበል ጀመሩ። ከልብ መሻት የፈለቀች አንዲት ልቅሶ የእልፎችን ሳቅ አሸነፈች። ተቆጣጠረቻቸው። በልቅሶ የተጨመቀው ዐይን ያወጣው ዕንባ በሳቅ የተጨመቁ ዐይኖች ያፈለቁትን ዕንባ ዋጣቸው፤ የተገኘን ውኃ ኹሉ በጉልበቱ የዝናብ እንደሚያስመስል እንደ ደራሽ ጎርፍ በሳቅ የተገኘው ዕንባ ኹሉ በሚጡ ዕንባ ጉልበት እንደዚያ ኾነ...

"መቁረብ እፈልጋለሁ"

አሁን ሳቅ የለም - ማባበል ብቻ እንጂ። 'አይዞሽ በቃ' እያሉ ከልብ የሚያባብሉ ከንፈሮች ጉንጮቿ ላይም ያርፉ ነበር።



ሚጡ ቤት ስትገባ እንደውዳሴ ማርያም ቀኑን ሙሉ ስትደግመው የነበረውን ሐረግ ደገመችው፦

"መቁረብ እፈልጋለሁ"

ወላጆቿ ግራ ገባቸው። ቀልድም መሰላቸው። ለማረሳሳትም ሞከሩ። ሚጡ ግን ያነሣሣት መንፈስ ቅዱስ ነውና ዝም ልትል አንደበቷ አልታዘዘላትም።

"መቁረብ እፈልጋለሁ!"

አንደበቷ ብቻ ሳይሆን አካሏ በሙሉ በዚህ ፍላጎቷ ተቃኘ። ዐይኗ በዕንባ መቁረብን ለመነ። ጆሮዋ ሌላ ነገር መስማትን ናቀ፤ አፎች ኹሉ 'እናቆርብሻለን' የሚል የምሥራችን እንዲዘምሩም ተመኘ። እግሯ ቤተ ክርስቲያን እንጂ የትም የማይሔድ ኾነ። አፍንጫዋ የጸሎት፣ የምልጃ ዕጣንን መዓዛ እንጂ ሌላ ሽታ ከረፋው። እጇ ከቆረበች በኋላ ነጠላዋን አፈፍ አድርጎ ጸበል እስክትጠጣ አፏ ላይ ሊጫን ፣ አፏን ሊሸፍን ጓጓ - ጓደኞቿ እንደነገሯት - እንደዚያ። አንገቷ ካለ ክር መራቆቱ አሳፈረው። ግንባሯ መስቀል መሳለምን፣ ከንፈሯ ሥዕለ ማርያምን መሳምን ተመኙ። ጸጉሯ በሻሽ ተሸፍኖ፣ ትከሻዋም ነጠላ ተጣፍቶለት መዝሙር ማጥናትና ሰኞ ስትመጣ ከጓደኞቿ ጋር መዘመር የዘወትር ኅልሟ ሆነ። የሰውነት አካሏ ባጠቃላይ ኦርቶዶክሳዊነትን ሻተ፤ ጌታ የለኮሰው፣ ሐዋርያት ያቀጣጠሉት የሃይማኖት እሳት በማዕከለ ሰብእናዋ ተንቦገቦገ። (ሉቃ. 12፡49)። የሚጡ ኹለመና እንዲህ አለ፦

"መቁረብ እፈልጋለሁ፣ ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ!"

ይህ የሚጡ ልምምጥ ቃል ብቻ አይደለም - በዕንባ የተለወሰ ንጹህ ጩኸት እንጂ። ንግግር ብቻ አይደለም - ከደመና በላይ የሚወጣ ልመና እንጂ። ዝርው ድምጽ ብቻ አይደለም - ሳይበተን የሚያርግ ጸሎት እንጂ።

...እናም ወደላይ ወጣ። ከፍ ከፍ አለና ራማን አንኳኳ። ቅዱስ ገብርኤልም አስተናገደው።



የሚጡ ሰሞንኛ ውትወታ ግራ ያጋባቸው ወላጆቿ ከእሑዶች በአንዱ ሚጡን ይዘው ወደ ገዳሙ ሰንበት ትምህርት ቤት መጡ። ሚጡ ዛሬ ነፍሷን አታውቅም። በወላጆቿ ተይዛ ልክ እንደጓደኞቿ ወደ ቤተ ክርስቲያን መጣች። ኹሉነገሯ ጥርስ ሆኗል። ሰኞ ደርሶ ትምህርት ቤት የምታወራው፣ የምትፈጥረው የትረካ ድባብ በሰንበቱ ታያት።

ወላጆቿ የሆነውን ኹሉ ለሰንበት ትምህርት ቤቱ መምህራን ነግረው "እባካችሁ ሚጡ እንድትቆርብ አድርጉልን" አሉ። ሚጡም "መቁረብ እፈልጋለው!" አለች በጥዑም አንደበቷ።

መምህራኑ ግን አንድ ሰው ለመቁረብ የሚያስፈልገውን ትምህርት መማር እንደሚቀድምና ወላጆቿም በቁርባን ጊዜ በመቅደስ መቆየት እንደማይችሉ አስረዷቸው። ሚጡም የዚያኑ ቀን እንደማትቆርብ ተረዳችው። አንድ ነገር ግን ገብቷታል - ኦርቶዶክስ ካልሆነች በገዳሙ መቁረብ እንደማትችል።

ስለዚህ ድምጿን ከፍ አድርጋ "ኦርቶዶክስ መሆን እፈልጋለሁ" አለች። ወላጆቿ ደንግጠው ተያዩ። በድምጿ ውስጥ ያለው ቆራጥነት እናትና አባቷን ለመተው እንኳን ደግማ የማታስብ አስመስሏታል።

መምህራኑ ሚጡንም ወላጆቿንም አረጋግተው ክትትላቸውን ቀጠሉ። የደብሩ ካህናትም ጉዳዩን ሥራቸው አደረጉት።



ከዕለታት ለሚጡ በተቀደሰች አንዲት እሑድ እንዲህ ኾነ....
የሚጡ ወላጆች ከመምህራኑ እንደተነገራቸው ቅዳሴ ሳይጀመር በሌሊት የገዳሙ ግቢ ውስጥ ተገኙ። መምህራኑ እየመሯቸው ወደ ክርስትና ቤት ሔዱ....

ከቆይታ በኋላ ወጥተው ወደ ቤተ መቅደስ ገቡ። ሚጡ የአንድ ሰውን እጅ ይዛ የቤተ መቅደሱ በር ጋር ደረሱ። እንደተማረችው ጫማዋን አውልቃ ተሳለመች፤ ወደ ውስጥ ገባች። አብረዋት ያሉትም ገቡ። ወላጆቿም ከመግባት አልተከለከሉም።

"ፃዑ ንዑሰ ክርስቲያን" ተባለ። ወላጆቿ ግን አልወጡም።

ልዑካኑ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ይዘው ከመቅደስ በክብር ወደ ቅድስቱ ተገለጡ። እንደተለመደው ብዙ ቆራቢያን ተሰለፉ። ሚጡም ሰልፉን ከሠሩት ተነሣህያን ጋር በመኾን ከበረች።

ከትምህርት ቤት ጓደኞቿ መካከል በወላጆቻቸው ታጅበውሊቆርቡ የተሰለፉም አሉ። ዛሬ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚጡ ተበለጡ። በርግጥ ሚጡ በልጅነት ጥምቀት ከብራ፣ በምሥጢረ ሜሮን መንፈስ ቅዱስን ተቀብላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመቁረብ መቅረቧ ነው። ጓደኞቿ ግን ደጋግመው በሥጋ ወደሙ ከብረዋል። ግን ኹሉም ብቻቸውን ናቸው።
1.6K views ቀላያት, 09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 10:34:49 ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ትውልዱ ከነገደ አሴር ሲሆን ትንሳኤ ሙታን የለም ብለው ያምኑ ከነበሩት ከሰዱቃውያን ወገን ነበር፡፡ ቶማስ በዕብራውያን፣ በአረማይክ ቋንቋ ዲዲሞስ በሕንድ ቋንቋ ማድረስ ማለት ሲሆን ትርጉሙም ፀሐይ ማለት ነው፡፡የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የተወጋ ጎኑን፣ የተቸነከሩ እጆቹን ካልዳሰስኩ አላምንም ያለ ሐዋርያ ነው ዮሐ 20፡25፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶ ቶማስ በእምነት እንዲጠነክር አስቀድሞ ቶማስ በሌለበት እንደተገለጠ ዳግመኛ ቶማስ ባለበት በዝግ ቤት ውስጥ ተገልጦ ቶማስ ያለው ሁሉ እንዲፈፀምለት አደረገ፡፡ ቶማስም ‹‹ጌታዬ አምላኬ ብሎ አምኖ መስክሯ፡፡ ከሐዋርያት ሁሉ ርቆ ወደ ምስራቅ የተጓዘ ሐዋርያ ነው፡፡
ለደቀ መዛሙርቱ በ50ኛው ቀን መንፈስቅዱስ ከወረደላቸው በኋላ ያገለግሉት ዘንድ ዓለማቱን በሃገረ ስብከት ከፋፈሉ፡፡ የሐዋርያው ቶማስ ሃገረ ስብከቱ ሕንደኬ ነው፡፡ ወንጌል ለመስበክ ምክንያት ይሆነኛል ብሎ በመስፍኑ ሉክዮስ ቤት በሠላሳ ብር ተቀጥሮ መስራት ጀመረ፡፡ ሕንጻ ማነጽ ሐውልት መቅረጽ እችላለሁ አለ በዚህም መስፍኑ ቤተመንግስቱን ያንጽለት ዘንድ ለቶማስ ብዙ ገንዘብ ቢሰጠው መጸወተው
ሉክዮስም ከሄደበት ሲመለስ ይታነጻል የተባለው ሕንጻ የለም ሕንጻውስ ቢለው ድሆቹን አሳየው በሃብት ንብረትህ በሰማይ መንግስት ተሰራልህ ሲለው ነው፡፡መስፍኑም ተቆጣ ይህ ክፉ ባርያ ተጫወተብኝ ብሎ እጅ እግሩን አሥሮ ቆዳውን አስገፍፎ ስልቻ ሰፍቶ በአሸዋ ሞልቶ አሸክሞ ሲያዞረው የሉክዮስ ሚስት አዘነችለት በቃሉ ትምህርት ከልጆችዋ ጋር አምና ነበርና በድንጋጤ ወድቃ ሞተች፡፡ በአንተ ምክንያት ሞተች ስለዚህም ዳግመኛ ሚስቴ ትነሳና በአንተ ልመን የቃልህን ትምህርት ልቀበል አለው፤ ጌታ ቁስሉን አቀዝግዞለት ሕማሙን አስችሎት እርሷ ካለችበት ሄዶ በስልቻው ቢያስነካው ተነሳች በዚህም የእጁን ተዓምራት የቃሉን ትምህርት ሰምቶ ሉክዮስ አመነ ተጠመቀም፡፡
ከዚህም በኋላ ስልቻውን ተሸክሞ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወረ ድውያንን እየፈወሰ አእዛብን እያስተማረ እያጠመቀ ቀንጦፍያ ደረሰ ቀንቶፍያም ሰባት ልጆች የሞተበትን ሽማግሌ አዝኖ አገኘው ልጆቹንም ከሞት አስነሳለት የእጆን ተዓምራት የቃሉን ትምህርት እየሰሙ ብዙዎች በወንጌል አመኑ፡፡ ከልጅ እስከ አዋቂ ከባርያ እስከገ ዢ ከሕዝብ እስከ ንጉሥ ድረስ በዚህም ካህናተ ጣኦት ቅንዓት አደረባቸው ስለዚህም ከንጉሥ ከመኳንንት አጣልተው በዚች ዕለት በሰይፍ አስመተሩት
የጸሎቱ በረከት በእኛ ላይ ይደርብን!!!
1.3K views ቀላያት, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 10:34:10
968 views ቀላያት, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 17:11:20

998 views ቀላያት, 14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 10:47:23 በአብ ቀኝ ተቀመጠ

ጌታችን በዕርገቱ “በአብ ቀኝ ተቀመጠ” መባሉ ለእግዚኣብሔር ግራና ቀኝ ፥ታችና ላይ ኖሮት ሳይሆን ወደ ቀደመ ክብሩ መመለሱን በስልጣን እኩል መሆናቸዉን የሚያስረዳ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ፪፡፯ “ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰዉም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ዝቅ አደረገ። እንደ ሰዉም ሆኖ ራሱን አዋረደ” የሚለዉ ቃል ጌታችን በሥጋዌው ራሱን በፈቃዱ ዝቅ አደረገ እንጅ በክብር ከአብ ከመንፈስቅዱስ እንደማይለይ ያስረዳናል፡፡ በቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሰረት በአብ ቀኝ ተቀመጠ ማለት በሥልጣን አንድ መሆንን ያሳያል፡፡ ስለዚህም ነቢዩ ዳንኤል በትንቢቱ “በሌሊትም ራእይ አየሁ፤ እነሆም የሰው ልጅ የሚመስል ከሰማይ ደመናት ጋር መጣ፤ በዘመናት ወደ ሸመገለውም ደረሰ፤ ወደ ፊቱም አቀረቡት። ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ግዛትና ክብር መንግሥትም ተሰጠው፤ ግዛቱም የማያልፍ የዘለዓለም ግዛት ነው፣ መንግሥቱም የማይጠፋ ነው፡፡” (ዳን. ፯፡፲፫-፲፬) ሲል ተናግሯል፡፡
ስለዚህ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአብ ቀኝ ተቀመጠ ስንል በክብር በልዕልና ከአብ ጋር እኩል ነው ማለታችን ነው። ይህም ከተዋሕዶ በፊት ደካማ፣ በደለኛ እና ውርደት ይስማማው የነበረው የእኛ ሥጋ ከተዋሕዶ በኋላ ጸጋን የሚያድል፣ እውነተኛ ፍርድን የሚያደርግ፣ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር እኩል ሥልጣን ያለው እውነተኛ ፈራጅ አምላክ እንደሆነ ለመግለጽ ነው እንጂ በመለኮቱስ ከአብ ሥልጣን ዝቅ ያለበት የዐይን ጥቅሻ ያህል ጊዜ እንኳ የለም። “ቀኝ” የሚለው ቃል ኃይልን ቅድስናን ወይም ክብርን የሚያመለክት ነው ። ኃይልን ከመግለፅ አኳያ ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊት “የእግዚአብሔር ቀኝ ኃይልን አደረገች” (መዝ. ፩፲፯፡፲፭) ሲል ተናግሯል፡፡ ክብርም ከመግለጽ አኳያ “ጻድቃንን በቀኙ ያቆማቸዋል” (ማቴ. ፳፭፡፴፫)  እንላለን፡፡ ስለዚህም “የእግዚአብሔር ቀኝ “ማለት የእግዚአብሔር ኃይል ፣ ጽድቅ ፣ ክብር ማለት ነው፡፡ ይህም በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ ለምሳሌ ያህልም ያህልም የሚከተሉትን ማየት ይቻላል፡፡

ጌታ ጌታዬን፡- ጠላቶችህን ለእግርህ መቀመጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው። (መዝ. ፻፱፡፻)

ከእንግዲህ ወዲህ የሰውን ልጅ በኀይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይ ደመናም ሲመጣ ታዩታላችሁ አለው። (ማቴ ፳፮፡፷፬)

እነሆ፥ ሰማይ ተከፍቶ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ። (ሐዋ ፯፡፶፮)

ኀጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ፣ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፡፡ (ዕብ ፩፡፫)

በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፡፡ (ዕብ ፰፡፩)

እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና፡፡ (ዕብ ፲፪፡፪)


መፃሕፍት በዓለም ላይ ሁሉ እንደፈለግን መግባትና መውጣት እንድንችል የሚያደርጉን ቪዛ ያላቸው ፓስፖርቶች ናቸው። የየሀገሩን ወግና ልማድ ታሪክና ፍልስፍና፣ የሕዝቦችን አስተሳሰብና ባህሪ ወዘተ እንደልባችን እንድናይ እንድናውቅ የሚያደርጉን ከልካይ የሌለባቸው ዘላለማዊ ሀብቶቻችን ናቸው።
ለጥያቄዎና አስተያየትዎ @bsratbot
ለተጨማሪ ት/ት @atronss_bot
https://telegram.me/atronss
1.1K views ቀላያት, edited  07:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ