አንገቷን ፈጥርቄ ወዘዘዝኳት...ብርቱኳን እየሠነጠቁ ይገባበዙበት የነበረ ቢላዋ መሰለኝ ከአልጋው ጎን ካለ ጠረጰዛ ላይ አየሁ።አነሳሁት...።ልክ እንደፋሲካ ዶሮ አንገቷን በጥሼ ልጥለው ዝግጅ ሆንኩ።ግን ወዲያው ሀሳቤን ቀየርኩ።ምን አልባት እግዚያብሄር የዚህቺን ሴት ነፍስ ዛሬ ወደራሱ ሊወስድ ወስኖ እኔን እንደማስፈፀሚያ መሳሪያ እየተጠቀመብኝ ቢሆንስ...?የሚል ሀሳብ በምናቤ ተሠነቀረብኝ።ይቅርታ እጠይቀዋለሁ እንጂ በዚህ ጉዳይ ላይ ፈፅሞ እግዚያብሄርን ልተባበረው አልችልም። ወሰንኩ። ቢላዋውን ወለሉ ላይ ወረወርኩና እሷን ገፋታትሬ ከቤቴ አባረርኳት። በታሪኩ ተመስጬ‹‹እሼ ከዛስ ምን ተፈጠረ…?አግኝተሀት አታውቅም ?››ስል ጠየቅኩት