Get Mystery Box with random crypto!

መንግሥት የተመረጡ የህወሓት ወታደራዊ ዐቅሞችን ዒላማ ያደረገ እርምጃ እወስዳልው አለ አሻም ዜና | Asham TV

መንግሥት የተመረጡ የህወሓት ወታደራዊ ዐቅሞችን ዒላማ ያደረገ እርምጃ እወስዳልው አለ

አሻም ዜና |ነሀሴ 20፣ 2014 ዓ.ም

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ የፌደራሉ መንግሥት የተመረጡ የህወሓት ወታደራዊ ዐቅሞች ዒላማ ያደረገ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።

መንግሥት እስከ አሁን ድረስ ለሰላም በሩን ክፍት አድርጎ ቢጠባበቅም ህወሓት ጥቃቱን እንደቀጠለበት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገልጿል።

በመሆኑም የፌዴራል መንግሥት ያለ ቅድመ ሁኔታ ለመነጋገር የገለጸው ዝግጁነት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለህወሓት ቡድን ፀረ ሰላም ዕብሪት ምንጭ የሆኑ ወታደራዊ ዐቅሞችን ዒላማ ያደረገ ርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።

"ስለሆነም በትግራይ የምትኖሩ ወገኖቻችን በተለይም የህወሓት ወታደራዊ መሣሪያዎች እና ማሠልጠኛዎች ካሉባቸው አካባቢዎች ራሳችሁን እንድታርቁ ይመከራል።" ሲል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asham