Get Mystery Box with random crypto!

የፌዴሬሽን ምክር ቤት 12 ክልል እንዲቋቋም የሚያስችል ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ወሰነ፡፡ አሻም | Asham TV

የፌዴሬሽን ምክር ቤት 12 ክልል እንዲቋቋም የሚያስችል ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ወሰነ፡፡

አሻም ዜና |ነሀሴ 12፣ 2014 ዓ.ም

ምክር ቤት ነሀሴ 12 ባካሄደው 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 1ኛ አመት፣ በ1ኛ አስቸኳይ ጉባኤው በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ይኖሩ የነበሩ የ6 ዞኖችና የ5 ልዩ ወረዳ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በአንድ ክልል የእንደራጅ አቤቱታን ተቀብሎ ከመረመረ በኃላ ሕዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ውሳኔ ወሰናል፡፡

ህዘበ ውሳኔ የሚያካሄዱት ምክር ቤቱም የወላይታ፣ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የደቡብ ኦሞ፣ የጌዴኦ፣ የኮንሶ ዞኖች፣ እንዲሁም የደራሼ፣ የአማሮ፣ የቡርጂ፣ የአሌ እና የባስኬቶ ልዩ ወረዳ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ናቸው ፡፡

ቀሪዎቹ የሀድያ፣ ሀላባ፣ ከምባታና ጠምባሮ፣ ስልጤ፣ ጉራጌ ዞኖችና የም ልዩ ወረዳ በነባሩ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል አንድ ላይ የሚቀጥሉ ይሆናል ተብሏል፡፡
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asham