Get Mystery Box with random crypto!

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም አስቸኳይ ጉባኤውን እንደሚያካሂድ ተጠቆመ አሻ | Asham TV

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም አስቸኳይ ጉባኤውን እንደሚያካሂድ ተጠቆመ

አሻም ዜና |ነሀሴ 10፣ 2014 ዓ.ም

የምክር ቤቱ ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ተረፈ በዳዳ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም አስቸኳይ ጉባኤውን በምክር ቤቱ የጉባኤ አዳራሽ እንደሚያካሂድ አስታውቀዋል፡፡

እንደዳይሬክተሩ ገለጻ ምክር ቤቱ በአስቸኳይ ጉባኤው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የምክር ቤቱ አስቸኳይ ጉባኤ ከመካሄዱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ የምክር ቤቱ አራት ቋሚ ኮሚቴዎች ከአስቸኳይ ጉባኤው አጀንዳዎች ጋር ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ተናግረዋል፡፡

ሰሞኑን ከክልልነት አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ጥያቄዎች እየቀረቡ መሆኑ ይገለጻል፡፡

ጉባዔው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራልነ ከመባሉ በስተቀር ከክልልነት አደረጃጀቶች ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ስላሉ ጥያቄዎች ስለመወያየቱ በግልጽ የተባለ ነገር የለም፡፡
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asham