Get Mystery Box with random crypto!

ባልደራስ አቶ እስክንድር ነጋ በመንግስት ታፍነዋል ወይም ታስረዋል የሚል ጥርጣሬ የለኝም አለ፡፡ | Asham TV

ባልደራስ አቶ እስክንድር ነጋ በመንግስት ታፍነዋል ወይም ታስረዋል የሚል ጥርጣሬ የለኝም አለ፡፡

አሻም ዜና |ነሀሴ 09፣ 2014 ዓ.ም

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ነሐሴ 9 ቀን 2014 ዓ.ም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ፕሬዝዳንቱ እስክንድር ነጋ ከሐምሌ 16 ቀን 2014 ዓ.ም ወዲህ ቢሮ መግባት እንዳቆሙ አስታውቋል፡፡

አቶ እስክንድር ነጋ በባልደራስ ፓርቲ የተረጋገጠ የፌስቡክ ገፅ ”ራሴን ከፓርቲው መሪነት አግልያለሁ” ማለታቸው ይታወሳል፡፡

ፓርቲው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ”ቤተሰቦቻቸውን ለማውራት ችለናል፤ በመንግስት ታስሯል ወይም ታፍኗል የሚል ጥርጣሬ እንደሌላቸው” ገልጸዋል፡፡

አቶ እስክንድር ነጋ ከፓርቲው መሪነት ራሳቸውን ማግለላቸው በሀገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ጫና የሚያሳይ ነው ሲል ፓርቲው በመግለጫው ጠቅሷል፡፡

ተስሊም ሙሀመድ

(በምሽቱ የዜና ሰዓታችን መግለጫውን በዝርዝር እንድትመለከቱት ከወዲሁ እንጋብዛለን)
——————————
አዳዲስ መረጃዎችና የአሻም ቲቪ ዝግጅቶች እንዲደርሱዎት የአሻም ቤተሰብን ይቀላቀሉ
Facebook - https://www.facebook.com/AshamMediaTrading
Youtube. - https://www.youtube.com/channel/UCNhqoLI39f7u5Bb6Fe60ECQ
Telegram - https://t.me/Asham_TV
Twitter. - https://twitter.com/tv_asham