Get Mystery Box with random crypto!

የዲነል ኢስላም ነኝ 🌙🌙

የቴሌግራም ቻናል አርማ analmuslimi — የዲነል ኢስላም ነኝ 🌙🌙
የቴሌግራም ቻናል አርማ analmuslimi — የዲነል ኢስላም ነኝ 🌙🌙
የሰርጥ አድራሻ: @analmuslimi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 761
የሰርጥ መግለጫ

🍃አሰላሙ አሌይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ ኢባዱ ረህማን 🍃
🙄አሊም፣ ሸህ፣ ኡስታዝ፣ ሙፍቲም አይደለሁም፤ 🙄ነገር ግን ገና
ተማሪ ነኝ።
Telegram የምጠቀመው👇
💝አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» 💝የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ እና ሱናን ለማስፉፉት ነው💖
🍃🌺🍃
Join👉 @analmuslimi
#ሀሳብ_መስጫ @analmuslimibot

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-18 23:11:21 አደራ አደራ

*ይህ አብዛኞቻችን የምንፈፅመው ስህተት ነው*
አብዛኞቻችን አዛን እያለ ወሬ እናወራለን። የተከበሩት የአለማት ነብይ ሙሀመድ (ሱለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ) እንዲህ ይሉናል “አዛን ሲል ምንም ነገር መስራት አቁሙ። ቁርዐን መቅራት እንኳ ቢሆን። አዛን እያለ የሚያወራ ሰው ሲሞት የሸሀዳ ቃል አይገጥመውም፣
*መልዕክቱን ለወንድም እህቶቻችን ባገኘነው መንገድ እናስተላልፍ።

@finding_hubullah
122 viewsHALAL BOY , 20:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 21:36:02
አሁን እኛ ያለንበትን ደረጃ ስንቱ ይመኘዋል መሰላቹ ይሄን ቪድዮ ለአንድ ሰው ብቻ በመላክ ቢያንስ አንድ ሰው አላህን እንዲያመሰግን ሰበብ ይሁኑ
ለአንድ ሰው ብቻ :
@analmuslimi
279 viewsHALAL BOY , edited  18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 08:49:45
አሰር 3
ሰውኛ ትውልድ

የአሰር መድረክ በተለያዩ ርዕሶች ባለፉት ግዜያቶች በጣም የሚያማምሩ ሁለት መድረኮችን በማሰናዳት ሶስተኛ መድረኩን "ሰውኛ ትውልድ" በሚል መሪ ቃል በቀን 05/10/2014 ለማዘጋጀት ዝግጅቱን አጠናቋል።


እናም ፕሮግራማችንን ፕሮግራም እየጋበዝናችሁ፤ ምርታችሁን እና አገልግሎታችሁን ማስተዋወቅ ለምትፈልጉ ድርጅቶች እንዲሁም ግለሰቦች ለመቀበል በራችን ክፍት መሆኑን በዚው አጋጣሚ እናበስራቹሃለን ።


ያለፉትን የአሰር መድረኮቻችንን ለመጎብኘት ከታች ያለውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሊንክ በመጫን ይታደሙ።
https://youtube.com/channel/UC_bdh4Imk0EG44sgCuW6c6g



አዘጋጅ የሀዋስ መሰናዶ ት/ቤት ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ

@hpsmuslimjema

ስፖንሰር ማድረግ ከፈለጉ
0949410833
0963920243
0903325632
0972445669
ይደውሉልን
@hpsmuslimjema
337 viewsAemirel Mueminin, 05:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 22:50:06 ሙስሊም ነኝ!
ይሰማል?
ሙ..ስ...ሊ...ም
ነኝ!!
251 viewsHALAL BOY , 19:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 21:49:21 እዉነተኛ ታሪክ
 
የታሪኩ ርዕስ
#ፍቅር_እንዲህ_ነዉ_ወይ???

      #Part

ፀሀፊ #አሚር

     ፍቅር ....ፍቅር ማለት ምን ማለት ነዉ ??? ማንኛችንም ስለፍቅር ስንጠየቅ መልሳችን ሀሳባችንን መግለፅ አንችልም ...ፍቅርን ብዙ ጊዜ ተጠያቂዉ ፍቅርን ግለፅ ሲባል ሊገልፀዉ የማይችል ግዑዝ ነገር ነዉ፡፡ አንድ ሰዉ አፈቅርሻለሁ ወይም አፈቅርሀለሁ የሚባለዉን ድምፅ ከሌላ ሰዉ ሲሰማ ከበፊቱ ካለበት አንድ ደስታ ይጨምራል ...ግን አፈቅርሻለሁ ያለዉ ሰዉ...ፍቅር ምንድን ነዉ ብለህ ስጠይቀዉ እንጃ ስለፍቅር መግለፅ አልችልም ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ ለመናገር ቀላል የሆነ ለመግለፅ ግን የከበደ ፍቅር ትርጉሙ ምንድን ነዉ ??? ትርጉም አልባ መልስ ያስተናግዳል፡፡
     ስለፍቅር እናንተ ምን አመለካከት አላችሁ???ፍቅር ማለት ዛሬ ተዋወቁ ነገ ተዋደዱ ከዛ ተጣሉ ..ከዛም አለቀሰ አለቀሰች ታረቁ ..ከዛስ............ይቀጥላል ሆነ ነገሩ፡፡ ፍቅርን በአፍህ መግለፅ ካልቻልክ መግለፅ ያልቻልከዉ ሶስት ፊደላት አሉ እነሱም ፍ...ቅ.....ር አይነቱ ይለያይ እንጂ በማንኛዉም ሰዉ ዉስጥ ያለ ነገር ነዉ ...ነገር ግን የፍቅር አይነቶች የተለያዩ ናቸዉ ፍቅርን በሰዉ ልጅ ብቻ ማመሳሰል አይቻልም፡፡
   ግን .ፍቅር ማለት ምን ማለት ነዉ??? እኔም ትርጉሙ ይጠፋኛል ፡፡ከፍቅር ሁሉ ከባድ ግን የወደዱትን ሰዉ ለራስ እንደማይሆን ለእሱ መስዋአትነት ከፍለን የሌላ እንደመሆን የሚያሳዝን የለም፡፡ ወንድ ልጅ ፍቅሩ ከላይ ነዉ የሚሉ ወገኖች አሉ ..የወንድ ልጅ ፍቅር ግን እስከ ጥግ እንደሚሄድ እና ወንድ ልጅ ባህሪዉ ሴትን የማያምንበት ምክንያት መጀመሪያ በሴት ልጅ ፈተና ተለክፎ ሁኖ ሊሆን ይችላል  .......
    ግን ይሄ ትርጉሙን በአፋችን መግለፅ የማንችለዉ ፍቅር የሚለዉ አንድ መልስ አለዉ መልሱም....የመጀመሪያዉ ፍቅርን ካመጣዉ ..ፍቅር የሚባልን በሰዉ ልጅ ላይ ካስቀመጠዉ ..ከፈጣሪህ ከአላህ ፍቅር ስጀምር...ምንም ፍቅር የሚባል ቢመጣብህ ከፈጣሪህ ፍቅር በላይ እንደማይሆን 100% እርግጠኛ ሁን(ኚ)
     ታሪኬን ከስሜ ልጀመር ከድር መሀመድ አህመድ ይባላል የተወለድኩት ደቡብ ወሎ ሀርቡ ከተማ ነዉ፡፡ ቀጠን ብየ በባህሪም በመልክም ሸጋ የሆንኩ ልጅ ነኝ ... የቤተሰቦቼ አኗኗር በጣም ድሆች ስንሆን ግን በቀዷ እና ቀድር የምናምን በአለን ተብቃቅተን የምናድርD ነን፡፡ የምንኖረው መንግስት በሰጠን በቀበሌ ቤት ነው፡፡ አባቴ ስራ አይሰራም .... እናቴም ብትሆን እድሜዋ ከ 60-70 ይደርሳል፡፡ታላቅም ታናሽም ወንድሞች አሉኝ፡፡
 
ሀርቡ ከተማ ለደሴ ደግሞ የ 20 ብር ትራንስፖርት ሲሆን ርቀቱ 40 ኪ.ሜ ገደማ ነው ወደ ኋላ ስንመላስ የሀፊዞች የጀግኖች ሀገር ከሚሴ ታዋስነናለች ርቀቱ 30 ኪ.ሜ ሲሆን ለአዲስ አበባ ደግሞ 345 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ 
    ሀርቡ የአየሯ ፀባይ ወይና ደጋ ነው ለአኗኗር በጣም ይመቻል ..በተጨማሪም
ሀርቡ የሸንኮራ አገዳ''ወደ አዲስ አበባ ወደ  አፋር ትልካለች፣የቦርከናን ወንዝ በአግባቡ መጠቀም ቢያቅታትም የአትክልት ና የፍራፍሬ ከተማ ናት።
''ሀርቡ ሌላ አንድ የተፈጥሮ ሀብት አለት።በከሀርቡ ከተማ  በግምት 8,ኪሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ፍልዉሀ አላት
ፍሉሀውን የውጭ ሀገር ዜጎች ሳይቀር እየመጡ ህመማቸውን''ይፈወሱበታል፡፡
    እድሚየ ሲደርስ እንደማንኛዉም ተማሪ የተማርኩ ሲሆን፡፡ የትምህርት ቤት ህይወቴ ብዙም ትኩረት የለኝም ነበር  :: .ከ1 እስከ 8 ሀርቡ አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ሲሆን 9 እና 10 ደግሞ ሀርቡ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ነዉ፡፡
   የአላህ ፈቃድ ሁኖ ወደ ዲን አለም የገባሁት በልጅነቴ ነበር..አባቴ ዲኔን እንድይዝ እንጂ ብዙም ለአካዳሚክ ትምህርት ትኩረት የለዉም ነበር.... ገና የሶስተኛ ክፍል ተማሪ ሁኜ ቁርዐን አክትሚያለሁ፡፡ ከዛም በየደረጃወ ኪታብ እየቀራሁ አደኩኝ፡፡ የፊቂህ ደርስም ቢሆን የሻፊኢን መዝሃብ ሰፊና ሹጃአ ባፈድል እያልኩኝ .... ሶርፍ ጀመሬ ነው የትውኩት .....
    ቁርዐን ተፍሲርም ጓደኛየ ጋር አብሬ ቀርቻለሁ፡፡ ሃዲስ እንቀራለን ኡሱሉ ሰላሳ ,,ኪታቡ ተውሂድ,, አርባ ሃዲስ ,,ቡልገል መራም ,,ሪያዱ ሷሊህ ,,ተጅሪድ ኢብነ ማጅህ እና ቡኻሪና ሙስሊም ቀርተናል
.....ተርቢያ የሚያደርገን ደግሞ የመስጅዳችን ሙአዚን ጀማል ዩሱፍ ይባላል ጎልማሳ ወጣት ነው እሱ ቂርዐት የቀራው ገጠር ተቸግሮ እንደሆነና እኛ ከተማ እየኖርን ትምህርት እየተማርን በትርፍ ጊዜያችን ካልቀራን በአላህ ዘንድ እንደምንጠየቅ ይመክረናል ዳእዋ እንድናደርግ ይጎተጉተናል አረብኛ እንድንጽፍ የዳእዋ ኖት ራሳችን ከኪታብ አውጣተን እንድናዘጋጅ ያስተምረናል ያዘጋጀነውን ያርምልናል::
     ወንበር ላይ ያስቀምጠንና ከፊታችን ድንጋይ ደርድሮ ድንጋዩ ሰው እንደሆነ አስቡት ከዚያ ዳእዋ ማድረግ ጀምሩ ይለናል ብቻ ዳኢወች ሆንን ለመጀመሪያ ጊዜ ዳዕዋ ለማድረግ መስጅድ ስቆም አስታውሳለሁ ከፈጂር ሶላት በኋላ ነበር እጥር ምጥን ያለ ከ 5 ደቂቃ አትበልጥም ግን የመጀመሪያየ ሆኖም እየፈራሁ ያደረኩት ዳእዋ ሰውን በእንባ አራጨው ስጨርስም ብዙወቹ ማሻአላህ እያሉ ግንባሬን ይስሙኝ ነበር
.......ይህን ሳደርግ እድሜየ ገና 17 ነበር ታዲያ በዚህ ኡስታዝ ተርቢያ እየተደረግን ማን ይቻለን ለኢስላም ፍቅሩ አደረብን መስጊድ የማይመጡ ቁርአን ያልቀሩትን ማበረታታት ተያይዘንዋል፡፡ ቅዳሜና እሁድ በረፍት ጊዜያችን ሪህላ በየሰፈሩ ቤት እየቆረቆርን ዳእዋ እናደርጋለን
     አስታውሰዋለሁ አሪፍ ጊዜ ነበር ትምህርት ቤት በእረፍት ሰአት ዳእዋ ፕሮግራም ይዘን ከጓደኛየ ኑረዲን ጋር እየተቀያየርን ዳእዋ እናደርጋለን ኑረዲን ከእኔ በእድሜ ከፍ ይላል ሰለምቴ ነው የድሮ ስሙ ኤፍሬም ይባላል፡፡ ሴት ወንዱ ሙስሊም ክርስቲያኑ የትምህርት ቤት መስገጃ ቦታ ተሰባስቦ ዳእዋችንን ይሰሙ ነበር ሱሪ የለበሱ ክርስቲያን ሴቶች ሳይቀሩ ይታደማሉ ዳእዋው ሲያስለቅስ አብረው ያለቅሳሉ ምን አይነት አሪፍ ጊዜ ነበር ታዲያ በዚያን ጊዜ ፍቅር የማይታሰብ ነው፡፡
    አስታውሳለሁ ከትምህርት ቤት ስለቀቅ ከኛ ሰፈር በታች አዚዛ የምትባል ልጅ ልትተዋወቀኝ ፈልጋ አዚዛ እባላለሁ ስትለኝ ከክላስ የሮጥኩኝ ቤቴ ገባሁ፡፡ ላየኝ ሰዉ የመቶ ሜትር እሯጭ ወይም የማራቶን ተወዳዳሪ ነበር የምመስለዉ፡፡ መቅሰፍት የወረደብኝ እስኪመስለኝ ሴቶች አሰላሙ አለይኩም ቢሉኝ እንኳ ላብ በላብ ነበር የምሆነዉ፡፡ ሴት ጋር ወሬ ቀጥ ብሎ ማየት በጭራሽ አይታሰብም ፡፡ ቂራአትና ዳእዋ ትምህርት ብቻ ነበር እንቅስቃሴያችን
   አልሃምዱሊላህ ይህ ሁሉ የአላህ ጸጋ ነው ኡስታዝ ጀማልንም ሳላመሰግነው አላልፍም አብሶ አንድ ጊዜ ረመዳን ወር ላይ በ 27 ኛው ለይል ታላላቅ ኡለሞች ሳይቀር ዳእዋ ለማድረግ ፈልገው ሲቋምጡ ዛሬ ተረኛው ከድር ነው ብሎ ሚንበሩ ላይ እጀን ይዞ ያስቀመጠኝን አልረሳውም፡፡ እንደዚህ አይነት የአኼራ ወንድም የትም አይገኝም ብዙ ነገር በህይወቴ አበርክቶልኛል
   እሁድ ረፋድ ላይና ጅሙአ ከመግሪብ በኋላ መስጅድ ዳእዋ ፕሮግራም ይዞልኝ አደርግም ነበር ሁልጊዜ ለአላህ ብየ ስወደው እኖራለሁ፡፡ ከቂርአቴም ጎን ትምህርቴንም እየተማርኩ ነዉ 10 ኛ ክፍል ማትሪክ ተፈተን ውጤቱ ሲመጣ ግን ....

#part ➋ይቀጥላል

join
@analmuslimi
253 viewsHALAL BOY , 18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 18:39:24
አሰላሙ አለይኩ ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ዉድ የቻናላችን ቤተሰብ ያው እንደተለመደዉ ለናንተ አሪፍ እና ምርጥ የምንለዉን ታሪክ ይዘንላቹ ከች ብለናል እንዳያመልጣቹ #ፍቅር #እንዲህ #ነው #ወይ ደሞ የታሪኩ ርዕስ ነዉ ። ዛሬ ማታ 2.00 ላይ ይጠብቁን።
Join join
@analmuslimi
@analmuslimi
185 viewsHALAL BOY , 15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 17:54:58
ፈገግ የሚል ፊት
ችግር መከራ ሀዘን አያጋጥመውም ማለት አይደለም....!
ፈገግ የሚሉ ሰወች እነዚህን ችግሮች የመሸከም አቅም ስላላቸው ነው።
@analmuslimi
168 viewsHALAL BOY , 14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 17:54:24
እንግደል!!
ሂስዳችንን... ክፋት የቋጠረ ቅናታችን... ሞኛሞኝ ተግባራቶችን...ሰውን ለማደናቀፍ የተዘረጋ እግሮቻችንን...ለመማታት የተዘረጉ እጆቻችንን እንግደላቸው።
@analmuslimi
146 viewsHALAL BOY , 14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 17:54:24 # እንዴት_ታዝናለህ !...
ሌላው ለሌላ አካል እያጎበደደ፤አላህ አንተን መርጦ
እስልምናን ሰቶ ለርሱ ብቻ እንድታጎበድድ ፈቀደልህ!
እንዴት ታዝናለህ!...
ስንቱ በተከበረበት ተዋርዶ፤ረበል ዓለሚን ያንተን ወንጀልህንና ነውርህን ደብቆልህ
ለምን ታዝናለህ!...
ስንቱ ነው አንድ አፉን ሚመገበው ጎኑን
ሚያሳርፍበት ማደሪያ የሌለው፤አዛኙ ጌታህ ቤትህን በምግብና በመጠጥ
ሞልቶልህ ማደሪያ ሰጠህ
ስለምንስ ታዝናለህ!
ስንቱ ጤናውን አቶል ፤ራህማኑ አንተን ሰላም አደረገህ
አትዘን!
የሰው ፊት የሚገርፈው ሚለምን ስንቱ መሰለህ!?
ጀልሉ ግን አንተን ከሰዎች አብቃቃህ!
በፍፁም እንዳታዝን!
ከህመም ብዛት በስቃይ አይኑን ሳይከድን የተኛ ስንቱ መሰለህ!?፤ወዱዱ ላንተ
ሰላማዊ እንቅልፍን
ሰጠህ
ያጣሀውን አትመልከት ፤ያለህን ተመልከትና
(አልሃምዱሊላህ) በልና አላህም እንህ
ካላቸው ሰዎች ሁን....
" ﻭَﻗَﻠِﻴﻞٌ ﻣِّﻦْ ﻋِﺒَﺎﺩِﻱَ ﺍﻟﺸَّﻜُﻮﺭُ "
"ከባሮቼ በጣም አመስጋኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡"
[ሱረቱ ሰበዕ:13]
@analmuslimi
158 viewsHALAL BOY , 14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 17:54:24 አስደናቂ እውነታ

በቀን ለ1 ሰአት ብቻ ኤርፎን ብትጠቀም ጆሮህ ውስጥ ያለውን ባክቴርያ በ 700 እጥፍ ታበዛዋለህ፡፡

@analmuslimi
149 viewsHALAL BOY , 14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ