‹‹ #ጠላትህን_ውደድ›› ማቴ. 5፥45 ‹‹ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ›› ማቴ. 5፥43-45 የዚህኛው ሕግ ዋና መልእክት ፍቅር ነው፡፡ ይህን ሕግ የሰጠን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጠላቶችን በመውደድ እኛም እንዲሁ እንድናደርግ አስተምሮናል፡፡ ሰውን ሁሉ መውደድ የክርስትና ሕግ ነው፡፡ ይህ ሕግ ፍጹም የሚሆነው ደግሞ የሚያውቁትን ወዳጅን በማፍቀር ብቻ ሳይሆን ጠላትን በመውደድ በተግባር የተገለጠ እንደሆነ ነው፡፡ ክርስቶስ ሁሉንም በመውደድ በፍጹም ፍቅር እንደተገለጠ ክርስቲኖች ሁሉ ደግሞ ሁሉን በመውደድ ፍጹማን እንድንሆን ይህ ሕግ ግድ ይለናል፡፡ ማቴ. 5፥43-46 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ 188 viewsDaniel dendir ጎዶሊያስ 28 .., 09:17