Get Mystery Box with random crypto!

#የግጥም_ዓለም

የቴሌግራም ቻናል አርማ amde_melek_21 — #የግጥም_ዓለም
የቴሌግራም ቻናል አርማ amde_melek_21 — #የግጥም_ዓለም
የሰርጥ አድራሻ: @amde_melek_21
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4
የሰርጥ መግለጫ

#ውድ የቻናሉ አባላት ፦
√ በዚህ ቻናል የግጥም ልምምድ ይደረጋል።
√ ማንኛውንም ግጥም መላክ ይችላሉ።
√ግጥሞቻችሁን ለመላክ
@Zerea_Buruk13
√ ኅዳር ፳፮/፫/፳፻፲፬ ዓ•ም

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-05 08:37:23 #ሥዕለት_ሰሚው_ሽማጎ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ

•••
እግዚአብሔር ይመስገን ሰው አላጣንም። ሰው በሌለለበት ሰው የሆኑ ሰዎችን እግዚአብሔር አዘጋጅቷል። በገንዘብ መርዳት ስላልቻላችሁ እርዳታችሁ አያስፈልግም ማለት አይደለም ። ለሌሎች በማድረስ ከበረከቱ መሳተፍ ይቻላል። እመኑኝ ሙሉውን መሸፈን የሚችል ሰው ከመካከላችን ይኖራል። ሊቀ ሰማዕቱ ቅዱስ
#ጊዮርጊስ ቤቱን የሚሠራለትን ሰው አዘጋጅቷል። እናንተ Share ብቻ አድርጉ። ሌላ ነገር አላስቸግራችሁም። ደግሞ እኔ ችግራቸውን ስለማውቅ ነው እንጂ #በጎ አድራጊ አይደለሁም። ክርስቶስ በቸርነቱ የጠበቀኝ የኃጢአት ባርያ ነኝ። እናንተም በእኔ ቦታ ብትሆኑ የምታደርጉት ተራ ነገር ነው። የእናንተ ይህን ጽሑፍ አንብቦ እርዳታ ማድረግ ግን ትልቅ መታደል ነው።
•••
ዛሬ የምሥራች አለኝ። አንዲት እህቴ ስሟ
#ወለተ_ሕይወት ትባላለች። ራሷ ናት በቀጥታ የደወለችልኝ። የበኩሌን መርዳት እሻለሁ ብላለች። ስሟን ለመግለጽ የወደድኩት ጸሎት አድርጉልኝ ብላለች። ታዲያ ሰሞኑን ሱባኤ በመሆኑ ሁላችንም ውዳሴ ማርያም ፣ መዝገበ ጸሎት እንዲሁም መዝሙረ ዳዊት አድርሰን ስንጨርስ #ወለተ_ሕይወት በማለት ልናስባት ይገባል። በየ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱ ያላችሁ እህት ወንድሞቼ ፤ እናት አባቶቼ ይህችን እህታችንን በጸሎት አስቧት። በተለይ በአካባቢያችሁ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የቅድስት ኪዳነምሕረት እና የቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን የሚገኝ ከሆነ አደራ ለቀዳሲያኑ በሙሉ በጸሎት እንዲያስቧት አሳስቡልን። ምክንያቱም እርዳታውን የምታደርገው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ነው። የልቧን መሻት ይፈጽምላት ዘንድ በጸሎት አትርሷት።
•••
በእውነት ደስ ብሎኛል። እንዲህ ሰው ሲኖር ደስ ይላል። አሁንም ይቀጥላል። ቤተክርስቲያኑ በጣም ብዙ እርዳታ ይፈልጋል። ነገ በቪዲዮ በሰፊው እመጣለሁ። እስከዚያ ድረስ ግን በያላችሁበት Share በማድረግ ተባበሩን። እኔ በመጻፍ እናንተ Share በማድረግ ሌሎቹ በብር በመርዳት እንዲሁም በጸሎት በሃሳብ በመተባበር የእግዚአብሔርን ቤት እንሥራ። በዚህ ኑሮ 100 ብር ከካርድ ውጪ ምን ይሆናል? ለእግዚአብሔር ብትሰጡት ግን በረከቱ እጥፍ ድርብ ነው።
•••

አሁኑኑ ብር መላክ የምትፈልጉ ከሆነ
1000161193888 አገሬ ሁነኝ ሽቱ (AGERIE HUNEGN SHITU) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (
#የሽማጎ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ቤተክርስቲያን_አስተዳዳሪ_የሆኑት_የቀሲስ_መሐሪ_የባለቤታቸው_አካውንት_ነው

እኔን በቀጥታ ማግኘት ለምትፈልጉ
0910990644 (ዓምደ_ብርሃን)

"ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ የሰበሰብከው ገንዘብ ከህክምና አያልፍም! እግዚአብሔር የባረከልህ ድህነትህ ግን ጸጋ ነው!"


@AmdE_MeleK_13
በውስጥ ጻፉልኝ።
215 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, edited  05:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 08:37:02 ሰላም በያላችሁበት እንዴት ናችሁ? መልእክቱን Share እያደረጋችሁ። የምሥራችም አለ። አንድ ሰው ተገኝቷል።
36 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, 05:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 08:27:38 ወገን ስለ ሽማጎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጉዳይ ምነው ዝምታን መረጣችሁ ? ለሥጋዊ ነገር ሲሆን እንፈጥናለን። ለመንፈሳዊ አገልግሎት ለምን እንዘገያለን። የእግዚአብሔርን ቤት የሚሠራ እኮ እግዚአብሔር ነው። ለበረከት እንዲሁም ለድኅነተ ሥጋ ለድኅነተ ነፍስ ነው እንጂ! እግዚአብሔር ቤቱን ይሠራል። ከተሰጠን ላይ ብንሰጥ ችግር አለው? ካህናቱ ያለ ደመወዝ እያገለገሉ ነው። በኢኮኖሚ ደግሞ የገጠር አራሽ ቀዳሽ ናቸው። በእውነት እነዚህን ካህናት #መርዳት ነው ከጥያቄ የሚያድነን። በኋላ ብቸገር አልረዳችሁኝም ብሎ ነው ጌታ የሚጠይቀን።
•••

ምናልባት ዕድሉ ገጥሟችሁ ቦታውን ብታዩት ደስ ይለኝ ነበር። የእውነት ካህናቶቹ እንደ ጸጋ_ዘአብ ትሕትና ገንዘባቸው ነው። ቁጥራቸው 5 ቢሆኑም ፍቅራቸው ግን እልፍ ነው። የዛሬን አያድርገውና ሙሉ ጽጌን ከዚሁ ቤተክርስቲያን ነበር ያሳለፍኩት። እኛም እንግዳ ተብለን ለእኛ ብለው ድግስ ያዘጋጁ ነበር። በእውነት ከዚህ በረከት ተሳተፉ። እሽ ቢያንስ እንኳን ሃሳብ ስጡ። ለሌላ ነገር ከምንሯሯጥ ለሚጠቅመን እንሩጥ።

#ሽማጎ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሥዕለት_ሰሚው!
332 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, 05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 19:34:14

102 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, 16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 10:26:46

160 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, 07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 08:03:54
ስለ ሽማጎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ሃሳባችሁን ሰንዝሩ። የግድ በብር ብቻ እርዳታው አይወሰንም። በሃሳብም መርዳት ይቻላል።
160 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, 05:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 11:27:46 እግዚአብሔር ይመስገን ብዙ ልጆችን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለማነጋገር እየሞከርን ነው። የባንክ ሰራተኞች ናቸው። ሁሉም በይሁንታ ተስማምተዋል። ለክርስቲያኖች ዓሥራት በኩራት ማውጣት ግዴታ ነው። ስለዚህ ይህንን ዓሥራት በኩራት በባንክ አካውንት በማስገባት በአንድ አሰባስበን #ለሽማጎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መላክ ነው። እግዚአብሔር ይመስገን ያሰብነው ከተሳካ ጭራሽ ለካህናቱም ደመ_ወዝ መክፈል እንችላለን! በየወሩ ባንችል እንኳን በየሦስት ወሩ ደመ_ወዝ መክፈል እንችላለን! ስለዚህ ሁላችሁም የመንግስትም ሆነ የግል ሰራተኞች #ዓሥራት በኩራታችንን ለሽማጎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን " በሚል መሪ ቃል እንረባረብ። አካውንቱን እኔ ራሴ እንዲከፈት አደርጋለሁ! ከሊቀ ካህናት ቀሲስ መሐሪ ጋር ስልክ እንደዋወላለን። እናንተም ከፈለጋችሁ 0933142862 #ዓምደ_ብርሃን ነው ስልካችሁን የሰጠን እያላችሁ ማውራት ትችላላችሁ። ሃሳብ አስተያየት እቀበላለሁ።
821 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, edited  08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 11:21:06 በጣም አስቸኳይ የበረከት ስራ

የሰማእቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ወዳጆች የሆናችሁ ይህ በረከት እንዳያመልጠን... የ5 ብር ካርድ ከ5 ደቂቃ በላይ አያዋራም ለጊዮርጊስ የምናወጣት 5 ብር ግን እስከ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ድረስ ታነጋግረናለች ምህረት እና ይቅርታን ታስገኝልናለች....

ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ

ይህችን መልእክት የምታነቡ ሁላችሁም የበኩላችሁን ተባበሩኝ መልእክቱ የኔ ሳይሆን የሊቀ ሰማእታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ነው ...

ወደ ጉዳያችን ልግባና በቡሬ ወረዳ ሽማጎ በተባለች ትንሽየ ሰፈር ውስጥ የሰማእቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በሚገርም ሁኔታ ተጠናቆ ...ግን አንዳንድ ያልተሟሉ ነገሮች አሉ።

ለምሳሌ ብነግራችሁ 2 ካህናት እና 3 ዲያቆናት ብቻ ናቸው ያሉት... እነዚህም ያለምንም ክፍያ ነው የሚያገለግሉት። በዚያ ላይ ደግሞ የክብረ በዓል ጊዜ ሊቃውንቱ ማኅሌቱን ሲቆሙ ጸናጽል የለም። መቋሚያ የለም። ...እነዚህ እና መሰል ችግሮች ስላሉ የእኛን ኪስ ይመለከታሉ። አስቡት እኛ አቅም ላይኖረን ይችላል። ግን እመኑኝ ይህንን መልእክት ሼር በማድረግ ብትተባበሩኝ ግን ልዑል እግዚአብሔር መፍትሄ አያሳጣንም። እኛም ደግሞ ከ5 ሳንቲም ጀምሮ እስከ ≥10 ብር ለእግዚአብሔር ዓሥራት በኩራት ብናወጣ ምን ያክል ጽድቅ ይሆንልን??

እውነት እላችኋለው ሰው በሌለበት ሰው ሆኖ መገኘት እንዴት አይነት መመረጥ መሰላችሁ?? እርግጠኛ ነኝ ሁሉን የሚያውቅ እግዚአብሔር ነው። ያላችሁ በብራችሁ የሌላችሁ በጸሎታችሁ እና ሼር በማድረግ ታሪክ እንስራ! ብናውቀው ኖሮ የእግዚአብሔርን ቤት ለመስራትም ሆነ ለመርዳትም እኮ መመረጥ ያስፈልጋል። አስታውሱ የኢየሩሳሌምን ቤተ መቅደስ ሊሰራ የፈለገው ዳዊት ነበር። ግን አልተፈቀደለትም። ለሰሎሞን ነበር የተፈቀደለት።

"ስጡ ይሰጣችኋል በምድር ያላበደረ በሰማይ የሚያበድረው የለም ፣ በምድር ርኅራኄ ያላደረገ በሰማይ የሚራራለት አያገኝም ፣ በዚህ ዓለም ማደሪያ ሰጥቶ እንግዳውን ያልተቀበለ በዚያች በፍርድ ቀን የሚያሳድረው አይኖርም ፣ በምድር ንስሐ ካልገባ በሰማይ ንስሐ የለም....(ድርሳነ ሚካኤል ዘመስከረም)

ስንቅ እንያዝ በማይታበል ቃሉ ይምረናልና " "ለዘጸውዓ ስመከ ወለዘገብረ ተዝካረከ ወለሐነጸ ቤትከ እምህር ለከ ፣ ስምህን የጠራውን መታሰቢያህን ያደረገውን ቤተ ክርስቲያንህን ያነጸውን ይቅር እልልሃለው" ...እንግዲህ ለጠቢብ አንዲት ቃል ትበቃዋለች ሰማእቱ 7 ዓመት ተሰቃይቶ ያገኛትን ክብር እግዚአብሔር ስለሚወደን እንኩ ለእናንተም ይለናል....

=> እኔ ያሰብኩት የባንክ አካውንት በሰማእቱ ስም ይከፈት ከዚያ በኋላ ሁሉም ሰው የሚችለውን ያበርክት ምናልባት ይህንን መልእክት አይቶ ሙሉውን የሚሸፍን ሰው እንዳለ ማን ያውቃል? ወይም ሌላ የተሻለ አማራጭ ካለ እንነጋገር "ተናገር ወኢታርምም ተናገር ዝም አትበል"... አደራ በሰማእቱ ስም በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም በኮከበ ፋርስ ስም ብላችሁ እዚህ ላይ አስተያየት አስቀምጡልኝ ምን ማድረግ እንዳለብን እንድንነጋገር እፈልጋለው እንዳያመልጠን ሌሎች እንዳይቀድሙን እንፍጠን!!!
762 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, 08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 20:51:59

179 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, 17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 19:17:28 • ክፍል ፪ (2)
መዝሙር ዘዳዊት
መዝሙር 11_20
(
#አድኅነኒ)

አሁኑኑ ይለቀቃል።
ለሌሎች በማጋራት የበኩላችሁን ተወጡ!
184 views𐌴𐌱𐌽𐌴 𐌼𐌴𐌹𐌴𐌺 Ꙁ 𐌴𐍄Ⴙιορꙗ, 16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ