2022-08-23 03:30:16
@ ጎ ጃ ም
…………………………………………………
ጎ ጃ ም ማለት ምን ማለት ነው
……………………………………………………………………
@ ፈጣሪ ከጥፋት ውሃ በሗላ ለኖህ እዲህ ሲል ቃል ገባለት ። ከእንግዲህ ወዲያ ፍጥረት በጥፋት ውሃ አይጠፋም። የቃል ኪዳን ምልክት የሆነ ቀስቴንም በደምና ላይ አኖራለሁ ። ዘፍ9"
ኖህም አዳም ጥፋት አጥፍቶ ከተባረረባት ምድር
መኖር ጀመረ ። ስሟንም አዳም ከተባረረባት ምድር እግዛብሄር እራርቶልኝ ፈቀደልኝ ሲል
ጌታ ራራ ሲል ሰየማት። ከጊዜ በሗላም ፡ታ ፡
ን አውጥተው ጌራራ ተባለች ያሁኒት ጎጃም
ኖህ የተቀበረበት ጎንደር ፋሲለደስ ቤተ መግስት የተሰራበት ላይ ሲሆን የሚስቱ የእመት አይክል መቃብር በጭልጋ ነው ይባላል።
ከእመት አይከል መቃበር ላይ ታላቅ ዛፍ በቅሎበት ቅማቶችም ፀሎት ያደርሱበታል ይባላል
አፄ ፋሲል የነገሱ ግዜም አምላክ ሁሉን ነገር ገልጦላቸው የኖህ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በኖህ መርከብ አምሳል ቤተ መንግስት በኖህ መቃብር ላይ ሰሩ ። ጎንደር ማለት ጉንድ ሀገር ፡ ከሚል የግእዝ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም የአገር ራስ ፡ ማለት ነው። ከጥፋት ውሃ በሗላ ለሰው ዘር የተረፈው ፡ የአለም አገራት ህዝቦች ሁሉ አባት የሆነው ኖህ የተቀበረበት ስፍራ ነውና የአገር ራስ ትባላለች ።
@ በከነዓን ረሀብ በገባ ጊዜ አብርሀም ወደ አዜብ ምድር ፡ ኢትዮጲያ ፡ መጥቶ ፡ ከጌራራው ንጉስ ከአቤሜሌክ ጋር ተቀመጡ ። ዘፍ 20።
አቤሜሌክ በአፄ ቴድሮስ ዘመን እደነበሩት የጎዥም ደጃዝማች ተደላ ጓሉ ያለ ደግ ፡ በህዝብ ዘንድ የተወደደ ስለ ነበር አቤሜሌክ ሲሞት ህዝቡ ለመታሰቢያ ይሆን ዘንድ ጌራራ ይባል የነበረውን አበሜለከክ ሲሉ ሰይመውታል ። አበሜለክ ማለት ደግሞ አባት ማለት ነው ይላሉ ።
ብዙ ጥንታዊ በልሳን ግዕዝ የተፃፉ መጠሀፍት አበሜለክ ተብለው ተፅፈው እናገኛለን። የጎንደር ታሪክን መፅሀፍ የፃፉት ያሬድ ግርማ ሀይሌ የጎጃምን ስም አበሜለክ ብለው ፅፈውታል ።
ጥንታዊ ግብጣዊያን አባይ ፈልቆ የሚመጣልን ከአምላክ ዙፋን ስር ነው ብለው ያምኑ ስለነበር በዚህም የተነሳ ፡ ጎዣም፡ ተባለ ይላሉ።
ጎዣም ፡ ማለትም የአምላክ ምድር ፡ የአምላክ መፈጠሪያ ፡ ማለት ነው። አዳም የተፈጠረበት ምድር ነው ሲሉ ሊቃውንቱ ይተነትኑታል ።
ከክርስቶስ ልደት በፊት ወደ አማራ ምድር የመጣው ግሪካዊው አጥኝ ሄሮዱቱስ ፡ ጎዣም፡ ማለት የአምላክ ምድር ማለት ነው። ጎዣም የደጋጎች ፡ የበቁ ቅዱሳን መኖሪያ ናት ።ብሎ ጥፏል ።
አዳንድ ሰዎች ፡ጎዣም ፡ ከመባሉ በፊት ፈለገ ግዮን ይባል ነበር የሚሉም አሉ።
በገድለ ቅዱስ ዘርአብሩክ ተፅፎ እደምናገኘው ግን ፈለገ ግዮን የሰከላ ወረዳ መጠሪያ እንጂ የሙሉ ጎጃም መጠሪያ አይደለም።
አንድም ጎጃም ማለት ቃሉ አማረኛ ሲሆን ትርጉሙም ፡ ጎጇም ፡ ቤታም ፡ ቤተኛ፡ የስልጣኔ ምንጭ ማለት ነው ።
የሰው ልጅ በዋሻ ፡ የድንጋይ ቤት ሰርቶ በየዛፉ ሰሌን ሰርቶና ዘርግቶ በድንኳን ይኖርበት በነበረበት ዘመን ፡ ጎጃሞች፡ ግን ሳር አጭደው ፡ እጨት ቆርጠው ፡ ጎጆ፡ ቤት ፡ በመስራት የሰው ልጅ ቤት ሰርቶ እዲኖር አድርገዋልና ጎጃሞች ቤታሞች ቤተኞች ጎጇሞች የስልጣኔ ምጮች ይባላሉ።
የጎጃም ስሞች በቅደም ተከተል
@ጌታ ራራ
@ ጌራራ
@ አበሜሌክ
@ ጎዣም
በሗላም ፡ዣ ፡ ትቀርና ወደ ፡ ጃ፡ ተለውጣ ጎጆ ቤት ከአለም ቀድሞ የተሰራው ጎጃም ላይ ስለሆነ ጎጃም የተባለ ሲሆን ጎጃሞ ማለትም የአምላክ ምድር ፡ የአምላክ ፡መፈጠሪያ ፡ የስልጣኔ ምንጭ ማለት ነው።
፡
፡ ጎጃም የቅኔ መቀኛ የእውቀትና የጀግንነት መፍለቂያ የስልጣኔ ምንጭ ናት
፡
፡
፡
፡
፡
፡ ፡
፡
@yenbab_gets
178 views【Nati..B】, 00:30