አዞዎቹ ድል ቀንቷቸዋል !
የሀያ ስምንተኛው ሳምንት የ ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በ ባህር ዳር ስታዲየም መካሄዱን ሲቀጥል አርባምንጭ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል ።
ኢትዮጵያ ቡናን የገጠመው አርባምንጭ ከተማ በ አህመድ ሁሴን ግብ ጨዋታቸውን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አጠናቀዋል ።
አቡበከር ናስር ለኢትዮጵያ ቡና የመጨረሻ ጨዋታውን ያከናወነ ሲሆን በዘንድሮ የውድድር በቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ አስራ አራት ግቦችን አስቆጥሮ አምስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል ።
የዛሬውን ውጤት ተከትሎ አርባምንጭ ከተማ በ አርባ ነጥብ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ ። ኢትዮጵያ ቡና በ አርባ ነጥብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል ።በቀጣይ ኢትዮጵያ ቡና ከ ፋሲል ከነማ እንዲሁም አርባምንጭ ከተማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚገናኙ ይሆናል ።
@Alphasportet