Get Mystery Box with random crypto!

የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ስራው በትምህርት ተቋማት ላይ ሊካሄድ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡ | AHADU RADIO FM 94.3

የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ስራው በትምህርት ተቋማት ላይ ሊካሄድ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡
በተለያዩ ዘርፎች ላይ የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ይዘው የሚሰሩ ባለሙያዎች ቁጥር ቀላል የሚባል እንዳልሆነ በተደጋጋሚ ሲገለፅ የሚስተዋል ሲሆን በተገቢው መንገድ አጣርቶ እርምጃ የመውሰድ ስራው ከሁሉም አስቀድሞ በትምህርት ተቋማት ላይ ሊካሄድ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት ዶ/ር ዮሀንስ በንቲ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡
የሀሰተኛ ማስረጃ በሁሉም ዘርፎች ላይ የሚስተዋል ችግር እንደሆነ ገልጸው በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሲሆን ግን በፍጹም ተቀባይነት የሌለው ከመሆኑ ባለፈ በትውልድ እና በአገር ላይ በሂደት የሚያመጣው አደጋ ከፍተኛ እንደሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ይህንን ለመከላከል እና ተገቢውን መፍትሄ እንዲያገኝም ከትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን እና ከሁሉም ክልሎች የትምህርት ቢሮዎች ጋር ተቀራርቦ የመስራት ፍላጎት እንዳላቸውም ጠቁመዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24