Get Mystery Box with random crypto!

መንግስት ለሚዲያ ተቋማት እና ሞያተኞች ከለላ የማድረግ ሃላፊነት እና ግዴታ ባለመወጣቱ ዘርፉ ለአደ | AHADU RADIO FM 94.3

መንግስት ለሚዲያ ተቋማት እና ሞያተኞች ከለላ የማድረግ ሃላፊነት እና ግዴታ ባለመወጣቱ ዘርፉ ለአደጋ መጋለጡ ተገለጸ፡፡
ከጋዜጠኞች እስር እና አፈና እንዲሁም ሚዲያዎች ላይ ከሚደርሱ ጫናዎች አንጻር ከቅርብ ጊዚያቶች ወዲህ በርካታ ቅሬታዎች በተደጋጋሚ እየተነሱ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ አሐዱ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አማረ አረጋዊ በመንግስት በኩል ሚዲያን የሚቆጣጠረው አካል ከመንግስት ነጻ ሆኖ ተጠሪነቱ ለፓርላማ ይሆናል ቦርዱም በፓርላማው ይሾማል ተብሎ ከጸደቀ በኋላ መንግስት እራሱ ቦርዱን በመሾሙ ቅሬታ ማቅረባቸውን አስታውሰው እስካሁን ድረስ በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ እንዳልተሰጣቸው ተናግረዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ አክለውም በሃገራችን በሚዲያ ላይ የሚፈጠሩ ችግሮች የህግ ሳይሆኑ የአፈጻጸም መሆናቸውን ገልጸው መንግስት ለጋዜጠኞች እና ሚዲያው ከለላ ማድረግ ሲገባው አሁን ባለው ነባራዊ እውነታ ያንን እንደማይደረግም አንስተዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24