Get Mystery Box with random crypto!

ምርጫ ቦርድ በ4 ዓመት የስራ ሂደት ውስጥ የገጠመውን ችግሮች ቢያሳውቅ ለዲሞክራሲ ሽግግር በቀጣይ | AHADU RADIO FM 94.3

ምርጫ ቦርድ በ4 ዓመት የስራ ሂደት ውስጥ የገጠመውን ችግሮች ቢያሳውቅ ለዲሞክራሲ ሽግግር በቀጣይ ለሚሰሩ ስራዎች አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ፡፡
አጋጠመኝ ባሉት የጤና እክል ምክንያት የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ ብርቱካን ሚደቅሳ በገዛ ፍቃዳቸው ከተሰጣቸው ሀላፊነት ለመልቀቅ ጥያቄ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው፡፡
በቀጣይ በተቋሙ አሰራር ላይ ምን ስጋት የሚፈጥሩ ጉዳዮች አሉ ወደ ፊት የሚሰራው ስራ በምን መልኩ ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል ሲል አሐዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ጸሀፊ ዶክተር ራሄል ባፌን ጠይቋል፡፡
የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በ4 ዓመት ውስጥ በተቋሙ ያሉትን ጉድለቶች እና ክፍተቶች በጽሁፍ አሊያም በማንኛውም መንገድ ማሳወቅ ቢችሉ ለዲሞክራሲ ሽግግር፤ በቀጣይ ለሚሰሩ ስራዎች አስተዋጾ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
እስከ ወረዳ ድረስ በመውረድ 6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ፍትሀዊ ለማድረግ ጥረቶችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰው የነበሩ ማነቆዎችን ጨምሮ ተቋሙን ነጻ እና ገለልተኛ ማድረግ ያልተቻለበትን ምክንያት ለህዝብ እና ለሀገር ጥቅም ሲሉ ማሳወቅ እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24